ቱኒዚያ ህገወጥ የፍልስተኞች ጀልባ ሠርቷል ያለችውን ጣሊያናዊ ያዘች
የቱኒዚያ ባለሥልጣናት ወደ አውሮፓ ለመግባት የሚሞክሩ ህገወጥ ፍልሰተኞች የሚጠቀሙበትን ጀልባ በመስራት የተጠረጠረውን የ45 ዓመቱን ጣሊያናዊ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡
ግለሰቡ በጀልባ ግንባታ ፋብሪካ ውስጥ የሚሠራ መሆኑን በምስራቅ ቱኒዝያ የምትገኘው የሞናስቲር ከተማ አቃቤ ህግ ቃል አቀባይ ፋሪድ ጃሃ ተናግረዋል።
ከሜዲትሬኒያን ባህር ወደ አውሮፓ እንዲያሻግር ከፕላስቲክ የተሰራውን ጀልባ ግንባታ በማቀድ የተሳተፉ ሶስት ቱኒዚያውያንም...