በካሜሩን በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ጨምሯል
በካሜሩን የ91 ዓመቱ ፕሬዝደንት ፖል ቢያ በመጪው ዓመት በሚደረገው ምርጫ በድጋሚ እንደሚወዳደሩ እየተነገረ ባለበት ወቅት፣ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት በመጨመር ላይ ነው።
ባለፉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ ስድስት ጋዜጠኞች በታጣቂዎች ጥቃት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በርካታ ጋዜጠኞችና የሬዲዮ ጣቢያዎች እንዲዘጉ ታዟል።
በካሜሩን የሚዲያ ባለሙያዎች ትሥሥር እንዳለው፣ አራት የሚሆኑ አባላቱ ጠብመንጃ እና ገጀራ በታጠቁ ኃይሎች በመዲናዋ ያዉንዴ ጥቃት ደርሶባቸዋል።...