የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የዐዲስ ሹሞችን ምደባ በሚያደናቀፉ ላይ “ርምጃ እወስዳለሁ” አለ
በመንግሥታዊ መዋቅሩ ላይ ማስተካከያ እያደረገ መኾኑን ያስታወቀው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፣ የዐዲስ ሓላፊዎችን ምደባ ጨምሮ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ተግባራት የሚያደናቅፉ አካላትን “በሕግ እጠይቃለኹ ዕንቅፋት ከመፍጠር ይቆጠቡ” ሲል አስጠነቀቀ፡፡
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ትላንት ረቡዕ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ፣ “ሕዝቡን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ በኾነ መንገድ ለማገልገል ከላይ እስከ ታች የሚያደርገውን ክልላዊ የመዋቅር ማስተካከያ አጠናክሮ ይቀጥላል፤”...