በእስራኤል የዌስት ባንክ ጥቃት ቢያንስ 9 ሰዎች ተገደሉ
እስራኤል በዌስት ባንክ ባካሄደችው ጥቃት ቢያንስ ዘጠኝ ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የአካባቢው የጤና ባለስልጣናት ዛሬ ረቡዕ ገለጹ።
ፍልስጤማውያኑ የተገደሉት ዋነኛው ጥቃትና ግጭት በተካሄደባቸው እስራኤል በያዘቻቸው የተለያዩ የጄኒን እና ቱባስ አካባቢዎች ነው፡፡
እስራኤል ሃማስ እና እስላማዊ ጂሃድን ጨምሮ በኢራን በሚደገፉ የሂዝቦላ ታጣቂ ቡድኖች ላይ የምታካሂደው ወታደራዊ ዘመቻ ጨምሯል፡፡
እኤአ ከጥቅምት 2023 ጀምሮ በዌስት ባንክ ከ640 በላይ...