አምባሳደር ማሲንጋ ከትግራይ ክልል እና ከህወሓት አመራሮች ጋራ መወያየታቸውን የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ አስታወቀ
ለሦስት ቀናት ጉብኝት፣ ከትላንት በስቲያ ሰኞ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ.ም. መቐለ የገቡት በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ እና ከህወሓት ሊቀ መንበር ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ጋራ በተናጠል ተወያይተዋል።
ውይይቱን ፍሪያማ ሲል የገለፀው በአዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ፣ በትግራይና በአካባቢው ዘለቄታዊ ሰላምና መረጋጋት ለማምጣት፣...