በስልጤ ዞን ከስድስት ሺሕ በላይ ሰዎች በጎርፍ መፈናቀላቸው ተገለጸ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን ሁለት ወረዳዎች እና በማረቆ ልዩ ወረዳ አንድ ቀበሌ ውስጥ በተከሠተ የጎርፍ አደጋ፣ ከስድስት ሺሕ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን፣ ተጎጂዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ፡፡
በዞኑ በስልጢ እና በምሥራቅ ስልጢ ወረዳዎች የተከሠተው የጎርፍ አደጋ መንሥኤ፣ በሁለቱ ወረዳዎች ከስድስት በላይ ቀበሌዎች ሰሞኑን የጣለውን ከባድ ዝናም ተከትሎ፣ ለመስኖ አገልግሎት ተብሎ በማረቆ ልዩ ወረዳ የተገነባ ኢንደሾ ልንጫ የተሰኘ...