በምስራቅ ሱዳን በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት አንድ ግድብ ሲደረመስ በርካታ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም
በሱዳን ምስራቃዊ ቀይ ባህር ግዛት አንድ ግድብ ተደርምሶ ያሰከተለው ጎርፍ መኖሪያ ቤቶችን ማጥለቅለቁን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታውቋል። በርካታ ሰዎች የደረሱበት እንደማይታወቅም የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እላንት እሁድ በሰጠው መግለጫ አርባት የተሰኘው ግድብ መደርመሱን እና ከአደጋው መውጫ ያጡ ሰዎችን ለመርዳት እርዳታ ወደአካባቢው መላኩን አስታውቋል።
መግለጫው አክሎ በጎርፍ አደጋው ቢያንስ አራት ሰዎች መሞታቸውን የገለጸ...