በጠለምት ወረዳ 10 ሰዎች በመሬት ናዳ መሞታቸውን አስተዳደሩ አስታወቀ
በሰሜን ጎንደር ዞን በጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ እና ቅዳሜ በጣለው ከባድ ዝናም የተነሣ በተከሠተው የመሬት ናዳ፣ 10 ሰዎች መሞታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል፡፡
የዞኑ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰላም ይኹን ሙላት ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ ከሞት አደጋው በተጨማሪ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዎች ከአካባቢያቸው መፈናቀላቸውን እንዲሁም በቤት እንስሳት እና በሰብል ላይ ጉዳት መድረሱን...