የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ በኪቭ ከዜለነስኪ ጋር ተገናኙ
የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ጋር ዛሬ አርብ ኪቭ ውስጥ ተገናኝተዋል፡፡
ሞዲ ከዜለነስኪ ጋር የተገናኙት በሞስኮ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ከተገናኙ ሳምንታት በኋላ ነው፡፡
ዩክሬን ከሶቭየት ህብረት ከተለየች እኤአ ከ1991 በኋላ አንድ የህንድ መሪ ዩክሬንን ሲጎበኝ ሞዲ የመጀመሪያው ናቸው፡፡
ዜለነስኪ ሞዲ በዚህ ወር መግቢያ ላይ በሞስኮ ባደረጉት ጉብኝት አዝነው እንደነበር ተመልክቷል፡፡
ሞዲ...