የሸቀጦች የዋጋ ተመን “ውጤት አላመጣም” የሶማሌ ክልል ነዋሪዎች
የሶማሌ ክልል፣ በጂጂጋ ከተማ በተመረጡ ሸቀጦች ላይ የዋጋ ተመን ማውጣቱ፣ “የሚፈለገውን ውጤት አላመጣም” ሲሉ፣ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ግን፣ የዋጋ ተመኑ፥ “አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሬን ለመቆጣጠር አስችሎኛል፤” ብሏል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ፣ በምግብ እና በግንባታ ግብአቶች ላይ የተጋነነ የዋጋ ጭማሬ ተስተውሎ እንደነበር ያስታወቀው የጂጂጋ ከተማ ንግድ እና ትራንስፖርት ቢሮ፣ ለእነኚኽ የተመረጡ ምርቶች የዋጋ ተመን...