የሃማስ ልዑክ ስለተኩስ አቁም ለመነጋገር ወደ ካይሮ አምርቷል
በከፍተኛ የሃማስ ባለስልጣን ካሊል አልኻያ የሚመራው የሃማስ ልዑክ በሰሞኑ የተኩስ አቁም ንግግር ዙሪያ ከሸምጋዮች የቀረበውን ለመስማት ዛሬ ቅዳሜ ወደ ካይሮ አቅንቷል ሲል የፍልስጤማውያኑ ቡድን ባወጣው መግለጫ አመለከተ፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ እና የእስራኤል ልዑካን ከትላንት በስቲያ ሐሙስ እና ትላንት አርብ በተኩስ አቁሙ ስምምነት ዙሪያ ልዩነቶችን በመፍታት ላይ ያተኮሩ ስብሰባዎችን በካይሮ እንዳካሄዱ ሁለት የግብጽ የደህንነት ምንጮች እንደነገሩት ሮይተርስ...