ሶማሊያ አሁንም የኢትዮጵያ ወታደሮች በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ እንዲሳተፉ አትፈቅድም
የሶማሊያ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው አወዛጋቢ የመግባቢያ ስምምነት እስካልወጣች ድረስ፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከመጪው የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ በአጭር አጠራሩ አውሶም (AUSSOM) አካል እንዲሆኑ እንደማይፈቅዱ በድጋሚ አስጠነቀቁ፡፡
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዛ አብዲ ባሬ ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ካላቋረጠች ኃይሎችዋ የመጭው የአውሶም ተልእኮ አባል እንደማይሆኑ በዚህ ሳምንት ምቃድሾ ውስጥ ተናግረዋል፡፡
አውሶም...