በደሴ ከተማ እና በተሁለደሬ ወረዳ የመሬት መንሸራተት አደጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለጸ
በደሴ ከተማ እና በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተትና መስረግ አደጋ፣ከ400 በላይ ሰዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ መስፈራቸውን፣ የሁለቱም አካባቢዎች አመራሮች አስታወቁ።
የደሴ ከተማ የከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ፣ በአደጋው ቤታቸው የፈረሰባቸውንና ለአደጋው ተጋላጭ ይኾናሉ ተብለው የተለዩ ሰዎችን፣ በደረቅ ወይራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሰፍሩ ማድረጉን ገልጿል፡፡
በተመሳሳይ፣ በተሁለደሬ ወረዳ ቆርኬ በተባለ...