በኮንሶ ዞን ሦስት የማኅበረሰብ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስምንት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ
በኮንሶ ዞን በሰገን ዙሪያ ወረዳ ሰገን ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ ማንነታቸው ባልታወቁ የታጠቁ ግለሰቦች እንደተፈጸመ በተገለጸ ጥቃት፣ ሦስት የማኅበረሰብ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስምንት ሰዎች መገደላቸውን፣ የወረዳው አስተዳደር ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቋል፡፡
በአካባቢው ከፍተኛ የጸጥታ ችግር መኖሩን የገለጹት የጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ኩናሎ በበኩላቸው፣ ጥቃት አድራሾቹ “ከአጎራባቹ የደራሼ ወረዳ የመጡ ናቸው” መባሉን አስተባብለዋል፤ “በዞኑ...