የተመድ ልዩ መርማሪው አፍጋኒስታን እንዳይገቡ ታገዱ
በአፍጋኒስታን የታሊባን መሪዎች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ልዩ መርማሪ የሆኑትን ሪቻርድ ቤኔት “ፕሮፖጋንዳ አሰራጭተዋል” በሚል ወደ ሃገሪቱ እንዳይገቡ አግደዋል።
የታሊባኑ ቃል አቀባይ ዛቢሁላ ሙጃሂድ እንዳሉት ተመድን የሚወክሉት መርማሪ “በመሬት ላይ ያለውን ሁኔታ” ያዛባሉ፣ ለዓለም አቀፉ ማኅበረስብም “አሳሳች መልዕክት ያቀርባሉ ሲሉ ከሰዋል።
ከሁለት ዓመታት በፊት ታሊባን አፍጋኒስታንን መቆጣጠሩን ተከትሎ፣ ሪቻርድ ቤኔት በተደጋጋሚ ወደ...