በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ 22ሺሕ የሱዳን ስደተኞች ወደ ዐዲስ መጠለያ እየተዛወሩ ነው
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በኩርሙክ ጊዜያዊ መጠለያዎች የነበሩ 22ሺሕ የሱዳን ስደተኞች፣ በዚያው ክልል ውስጥ ወደተዘጋጀ የኡራ ቋሚ መጠለያ እየተዛወሩ መኾናቸውን፣ የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት አስታወቀ፡፡
በአገልግሎት ተቋሙ የአሶሳ ቅንርጫፍ ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ያሲን አሸናፊ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ ስደተኞቹ የነበሩበት የኩርሙክ ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራ፣ ዓለም አቀፍ መስፈርትን እንደማያሟላ ጠቅሰው፣ ዐዲሱ የኡራ መጠለያ...