ተመድ የረድኤት ሠራተኞች ጥቃት መብዛት እየተለመደ መምጣቱን አወገዘ
የተባበሩት መንግስታት "ተቀባይነት የሌለው" ያለው የጥቃት መጠን በሰብአዊ ሠራተኞች ላይ የተለመደ እየሆነ መጥቷል ሲል ዛሬ ሰኞ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።
“በዓለም ዙሪያ ጥቃት ከደረሰባቸው የረድኤት ድርጅቶች ሠራተኞች ውስጥ 280ቱ እኤአ በ2023 የተገደሉ ናቸው” ብሏል መግለጫው።
በጋዛ ያለው የእስራኤል-ሃማስ ጦርነት በዚህ ዓመት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ሠራተኞች ሞት ሊያባብስ እንደሚችልም የመንግስታቱ ድርጅት አስጠንቅቋል።
በተባበሩት...