ኬንያ ውስጥ ተቆራርጠው ተጥለው በተገኙት የሰውነት አካላት ጉዳይ የተያዘው ተጠርጣሪ ከእስር አመለጠ
42 ሴቶችን መግደሉን ያመነው እና ተቆራርጠው በተጣሉት የሰውነት አካላት ጉዳይ ‘እጁ አለበት’ ሲል በቁጥጥር ስር አውሎት የነበረው ተጠርጣሪ ከእስር ማምለጡን የኬንያ ፖሊስ አስታወቀ።
ኮሊንስ ጁማሲ ካሉሻ በወንጀሉ ተጠርጥሮ የተያዘው መርማሪዎች ክስ ከመመስረታቸው አስቀድሞ ወንጀሉን እንዲያጣሩ ፍርድ ቤት ሰባት ተጨማሪ ቀናት ከፈቀደላቸው በኋላ ነው። ሆኖም የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊው እንዳስረዱት፤ ካሉሻ ከሌሎች 12 እስረኞች ጋር በመሆን ዛሬ ማለዳ ላይ የእስር...