በኮንሶ ዞን ሦስት የማኅበረሰብ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስምንት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ
በኮንሶ ዞን በሰገን ዙሪያ ወረዳ ሰገን ከተማ ባለፈው ቅዳሜ በተፈጸመ ጥቃት፣ ሦስት የማኅበረሰብ አባላትን ጨምሮ ስምንት ሰዎች፣ ማንነታቸው ባልታወቁ የታጠቁ ግለሰቦች መገደላቸውን፣ የወረዳው አስተዳደር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡
በአካባቢው ከፍተኛ የጸጥታ ችግር መኖሩን የገለጹት የጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ኩናሎ በበኩላቸው፣ ጥቃት አድራሾቹ ከአጎራባቹ የዲራሼ ወረዳ የሔዱ መኾኑን ጠቁመው፣ “በዞኑ መንግሥት የሚደገፉ ናቸው፤” መባሉን “ሐሰት ነው”...