ራሳቸውን የሚያጠፉ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወጣቶች ቁጥር ለምን ጨመረ?
ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በየ11 ደቂቃው አንድ ሰው ራሱን እንደሚያጠፋ የአሜሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ መስሪያቤት መረጃ ያሳያል። ባለፈው ዓመት ብቻ ወደ 50 ሺህ የሚጠጉ አሜሪካውያን ራሳቸውን አጥፍተዋል። በተለይ እድሜያቸው ከ10 እስከ 24 ዓመት ባሉ ወጣቶች ዘንድ ደግሞ 62 በመቶ የጨመረ ሲሆን፣ በዛ እድሜ ክልል ለሚገኙ ወጣቶች ዋና የሞት መንስዔም መሆኑንም ተመልክቷል።
ይህ ቁጥር ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወይም ኢትዮጵያዊ-አሜሪካውያንን ወጣቶችም...