የካታሎኒያ መገንጠል መሪ ስፔይን ገብተው ወጡ
የካታሎኒያ ተገንጣይ መሪ ካርሌስ ፑችዴሞን በባርሴሎና በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከታዩ በኋላ ስፔይንን ለቀው ወደ ቤልጂየም ሄዱ።
የፓርቲያቸው ዋና ጸሀፊ ዛሬ ዓርብ በሰጡት መግለጫ ፑችዴሞን ስፔይን ውስጥ እንዲያዙ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸዋል ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ፑችደሞን ከሀገር በመሸሽ ራሳቸውን በግዞት በሚያኖሩባት ዋተርሉ ቤልጂየም ስለመድረሳቸው እንደማያውቁ ዋና ጸሀፊው ጆርዲ ቱሩል ተናግረዋል፡፡
እኤአ ካታሎኒያን ከስፔይን ለመገንጠል ያደረጉት ሙከራ...