የኢትዮጵያና የሶማሊያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሁለተኛ ዙር ውይይት ሊያደርጉ ነው
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የፈረመችው የባሕር በር አጠቃቀም ስምምነት የፈጠረውን አለመግባባት በተመለከተ፣ የኢትዮጵያና የሶማሊያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር በሚቀጥለው ሳምንት አንካራ ላይ ተገናኝተው ለሁለተኛ ዙር እንደሚወያዩ የቱርክ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን ዛሬ ዓርብ አስታወቀዋል።
ታኅሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ፣ ወይም በያዝነው የፈረንጆች ዓመት በመጀመሪያው ቀን፣ ኢትዮጵያ 20 ኪ/ሜ የሚደርስ የባሕር ዳርቻ ከሶማሊላንድ በሊዝ ለመያዝ ስምምነት መፈራረሟ፣...