ምርጫ ቦርድ ህወሓትን “በልዩ ኹኔታ” መዘገበው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ(ህ.ወ.ሓ.ት)፣ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ “በልዩ ኹኔታ” መስጠቱን፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ህወሓት፣ ዳግም ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስለት፣ በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ ያቀረበውን ጥያቄ ያስታወሰው ቦርዱ፣ በቀድሞው ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011ም ኾነ በተሻሻለው ዐዋጅ ቁጥር 1332/2016 መሠረት፣ በዐመፃ ተግባር ላይ ተሰማርቶ ሕጋዊ ሰውነቱ ለተሰረዘ ፓርቲ የቀድሞ ህልውናውን መልሶ የሚሰጥ...