ኒዤር ከዩክሬን ጋራ የነበራትን የዲፕሎማሲ ግንኙነት አቋረጠች
በማሊ የሚገኙ አማጺያን የሃገሪቱን ወታደሮችና የዋግነር ቅጥረኛ ቡድን አባላትን ባለፈው ወር ሲገድሉ አስፈላጊዎን መረጃ እንደሰጠች ዩክሬን ማስታወቋን ተከትሎ፣ በኒዤር የሚገኘው ሁንታ ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ማቋረጡን አስታውቋል።
የኒዤር ውሳኔ የመጣው ጎረቤት ማሊም ባለፈው እሁድ ግንኙነቷን እንዳቋረጠች ማስታወቋን ተከትሎ ነው። ዩክሬን የማሊን ውሳኔ “አርቆ የማያስብና ችኩል” ስትል ገልጻለች፡፡
ዲፕሎማሲያዊ ቅራኔው የተከሰተው የዩክሬን...