ባንግላዴሽ አዲስ ጊዜያዊ መሪ ሾመች
የባንግላዴሽ ኤታማዦር ሹም የኖቤል ተሸላሚውን ሙሃማድ ዩኑስ የሃገሪቱ ጊዜያዊ መንግስት መሪ ሆነው መመረጣቸውንና ነገ ሐሙስ ምሽት ላይ ከፓሪስ እንደተመለሱ ቃለ መሃላ እንደሚፈጽሙ አስታውቀዋል።
ኤታማዦር ሹሙ ጀኔራል ዌከር ዛማን፣ ሙሃማድ ዩኑስን በመሪነት የሾሙት የ300 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ተቃውሞ የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩትን ሼክ ሃሲና ሃገር ለቀው እንዲወጡ ማስገደዱን ተከትሎ ነው።
ተቃውሞው የተነሳው መንግስት ሥራን በኮታ ለመሥጠት በመወሰኑ...