AMHARIC.VOANEWS.COM
ባንግላዴሽ አዲስ ጊዜያዊ መሪ ሾመች
የባንግላዴሽ ኤታማዦር ሹም የኖቤል ተሸላሚውን ሙሃማድ ዩኑስ የሃገሪቱ ጊዜያዊ መንግስት መሪ ሆነው መመረጣቸውንና ነገ ሐሙስ ምሽት ላይ ከፓሪስ እንደተመለሱ ቃለ መሃላ እንደሚፈጽሙ አስታውቀዋል። ኤታማዦር ሹሙ ጀኔራል ዌከር ዛማን፣ ሙሃማድ ዩኑስን በመሪነት የሾሙት የ300 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ተቃውሞ የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩትን ሼክ ሃሲና ሃገር ለቀው እንዲወጡ ማስገደዱን ተከትሎ ነው። ተቃውሞው የተነሳው መንግስት ሥራን በኮታ ለመሥጠት በመወሰኑ...
0 Comments 0 Shares