ብሔራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107ነጥብ9 ብር ዋጋ መሸጡን ገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ዛሬ ባካሔደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107ነጥብ9 ብር ዋጋ መሸጡን ሲያስታውቅ፣ 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልጿል፡፡
ይህ የብሔራዊ ባንክ ርምጃ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያን ለማረጋጋት የሚወሰድ መኾኑን፣ የፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ተንታኝ የኾኑት ሽዋፈራሁ ሽታሁን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የዋጋ ንረት ተጽእኖን ለመከላከል ድጎማ ይደረግባቸዋል ከተባሉ የገቢ ምርቶች አንዱ...