በደቡብ ጎንደር ዞን የሦስት ወረዳዎች ነዋሪዎች በጎርፍ መከበባቸው ተገለጸ
በደቡብ ጎንደር ዞን ሦስት ወረዳዎች፣ ከባድ ዝናም መጣሉን ተከትሎ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በጎርፍ መከበባቸውን የገለጹ ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣናት፣ ከ15ሺሕ በላይ ነዋሪዎች አስቸኳይ የነፍስ አድን ሥራ እንደሚያስፈልጋቸው አመልክተዋል፡፡
የፎገራ እና የሊቦ ከምከም ወረዳ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ባለሞያዎች፣ ዛሬ ረቡዕ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ በሁለቱ ወረዳዎች በተለይ ከ12 በላይ የሚኾኑ ቀበሌዎች በጎርፍ መከበባቸውን...