በአሜሪካ የፖለቲካ ግድያ ለመፈጸም አሲሯል የተባለ ፓኪስታናዊ ተያዘ
ከኢራን ጋራ ግንኙነት ያለውና በአሜሪካ ውስጥ የፖለቲካ ግድያ ለመፈጸም አሲሮ ነበር ያሉትን አንድ ፓኪስታናዊ ይዘው ክስ መመስረታቸውን በብሩክሊን፣ ኒው ዮርክ የሚገኙ አቃቢያ ሕግ አስታውቀዋል።
አሲፍ መርቻንት የተባለው ግለሰብ ወደ ኒው ዮርክ በመምጣት ነፍሰ ገዳዮችንም ለመቅጠር ሞክሯል ተብሏል።
አሲፍ መርቻንት ግድያውን እንዲያከናውኑ የመረጣቸው ግለሰቦች ማንንነታቸውን የደበቁ የሕግ አስከባሪ አባላት መሆናቸውን እንዲሁም ቅድሚያ 5ሺሕ ዶላር እንደከፈላቸውም...