አሜሪካ ከሰሃራ በታች ላሉ ሃገራት 536 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የሰብዓዊ ርዳታ መደበች
የአሜሪካ መንግስት ከሰሃራ በታች ላሉ ሃገራት ለተጨማሪ የሰብዓዊ ሥራ የሚውል 536 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን ዛሬ አስታውቋል፡፡
ከተጠቀሰው ገንዘብ ውስጥ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የሰብዓዊ አጋሮች 97 ሚሊዮን ዶላር መመደቡንና ከዚህም ውስጥ 87 ሚሊዮን ዶላሩ ለስደተኞች የሚውል መሆኑን በአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የሰብዓዊ ደህንነት፣ ዲሞክራሲ እና ሰብዓዊ መብት ረዳት ፀሃፊ የሆኑት ኡዝራ ዜያ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ አስታውቀዋል።
ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት 38...