ዩናይትድ ስቴትስ: ለኢትዮጵያ የ97 ሚሊዮን ዶላር ሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች
ለአፍሪካ 536 ሚሊዮን ዶላር ዐዲስ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ ያደረገችው ዩናይትድ ስቴትስ፣ ከዚኽም 97 ሚሊዮን ዶላሩ ለኢትዮጵያ የተመደበ መኾኑን አስታውቃለች፡፡
በዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የሲቪሎች ደኅንነት የዴሞክራሲ እና ሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ዑዝራ ዘያ፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ነሐሴ 2 ቀን 2016 ዓ.ም. በዐዲስ አበባ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ በሰጡት መግለጫ፣ ዐዲሱን የዩናይትድ ስቴትስ የሰብአዊ ድጋፍ ፈንድ ይፋ አድርገዋል፡፡
“ዛሬ...