የቻይናው ሺ እና የጣልያኗ ሜሎኒ ቤጂንግ ውስጥ መከሩ
የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ እና የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በዩክሬን ጦርነት እና በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ዛሬ ሰኞ ቤጂንግ ውስጥ መወያየታቸውን የሜሎኒ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ሀገራቸው የወቅቱን የቡድን 7 ፕሬዚዳንትነት ቦታ የያዘችው ሜሎኒ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ዓለማቀፋዊ የጸጥታ ችግርን ለመቋቋም ቻይና እንደ አጋር ያላትን ጠቀሜታ በንግግራቸው አሳስበዋል።
ሁለቱ መሪዎች "ከዩክሬን ጦርነት ጀምሮ በመካከለኛው ምስራቅ...