በተከዜ ወንዝ ላይ በደረሰ የጀልባ አደጋ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ
በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ ከሰሃላ ሰየምት ወደ ዝቋላ ወረዳ በተከዜ ወንዝ ላይ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ በደረሰበት አደጋ፣ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 10 ሰዎች የደረሱበት እንዳልታወቀ፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት ገለጹ።
የሰሀላ ሰየምት ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ብሩ፣ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ አደጋው የደረሰበት አነስተኛ ሞተር አልባ ጀልባ “ከልክ በላይ ተጓዦችን የጫነ ነበር፤” ብለዋል፡፡
እስከ አሁን በአደጋው የሞቱ...