ኬንያ የተቃዋሚዎችን መብት እንድታከብር አሜሪካ ጠየቀች
በኬንያ የታክስ ጭማሪን በመቃወም በተደረጉ ሰልፎች ላይ ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ፣ መንግስት ሰላማዊ የሆነ ተቃውሞ የማድረግን መብት እንዲያከብር አሜሪካ ዛሬ ረቡዕ ጥሪ አድርጋለች፡፡
“ሠላማዊ ሕዝባዊ ስብሰባ የማድረግ መብታቸውን በመጠቀም ላይ ያሉ ኬንውያን አደጋ ላይ እንዳይወድቁ ጥንቃቄ እንዲደረግ መወትወታችንን እንቀጥላልን” ሲሉ የአሜሪካው ብሔራዊ የደህንነት ም/ ቤት ቃል አቀባ ጃን ከርቢ ለዜና ሰዎች ተናግረዋል።
“መብቱ በኬንያ ሕገ...