በሱዳን ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝብ የከፋ የምግብ ዋስትና ዕጦት ገጥሞታል
በጦርነት በመታመስ ላይ ባለችው ሱዳን 25.6 ሚሊዮን የሚሆነው ወይም ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝብ የከፋ የምግብ ዋስትና ዕጦት እንደገጠመው አንድ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የወጣ የጥናት ሪፖርት አመልክቷል።
የምግብ ዋስትናን ደረጃ የሚያወጣውና (IPC) በመባል የሚታወቀው መለኪያ እንዳመለከተው፣ 755 ሺሕ የሚሆኑ ሰዎች ረሃብ የገጠማቸው ሲሆን፣ 8.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር፣ ከ 14...