በሜክሲኮ የቮልክስዋገን አፍቃሪዎች ሰልፍ አደረጉ
በሜክሲኮ ‘ቢትል’ የተሰኘችው የቮልክስዋገን ሞዴል አፍቃሪዎች፣ በሞዴሏ ዓለም አቀፍ ቀን በሆነው በትላንትናው ዕለት መኪናቸውን ይዘው ሰልፍ አድርገዋል።
በሜክሲኮ ‘ቮቾ’ ሲሉ የሚጠሯት ሞዴል፣ በኢትዮጵያም በብዛት ትታይ የነበረና አሁንም አጋጊጠው የሚነዷት እንዳሉ ይታወቃል።
አሮጌዋ ሞዴል ባላት ለየት ያለ ቅርጽ ተወዳጅነት በማትረፏ፣ በመላው ዓለም በሚገኙ ከተሞች በብዛት ትታይ ነበር።
ቢትል “የሕዝብ መኪና” ለመባልም በቅታ ነበር። በሜክሲኮ አሮጌዋ ሞዴል...