በናይሮቢ ፖሊስ ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ በተነ
የኬንያ ፖሊስ በቅርቡ የአገሪቱ ፓርላማ ያረቀቀውን መጠነ ሰፊ የግብር ጭማሪ የሚጠይቅ ረቂቅ የፋይናንስ ሕግ ለመቃወም በወጡ ሰልፈኞች ላይ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል።
ሰልፈኞቹ ወደ ፓርላማ እንዳይገቡ ለማድረግ ቁጥሩ የበዛ ፖሊስ ተሰማርቷል።
የኬንያ መንግስት ሃገሪቱ ያለባትን ግዙፍ ዓለም አቀፍ ዕዳ ወለድ ክፍያ ለመቀጠል ያስፈልገኛል በሚል ያቀረበውን ረቂቅ ሕግ በመቃወም ከቅርብ ቀናት ወዲህ በወጣቶች የሚመራ የማኅበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ በኬንያ እየጨመረ መምጣቱ...