በአቢጃን ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ሕይወት በመቅጠፍ ላይ ነው
በአይቮሪ ኮስት ትልቋ ከተማ አቢጃን በደረሰ የጎርፍና የመሬት መንሸራተት አደጋ ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ ቢያንስ 24 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል።
በአራት እጥፍ የከበደ ዝናብ የምዕራብ አፍሪካዊቱን ሃገር የኢኮኖሚ መዲና ሲመታ፣ ከፍተኛ ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ተከስቷል።
ከወዲያኛው ሳምንት ሐሙስ እስካለፈው ቅዳሜ በጣለው ዝናብ ቢያንስ 24 ሰዎች እንደሞቱ የሲቪሎችን ደህንነት የሚከታተለው መንግስታዊ ቢሮ አስታውቋል።
በጎርፍ የተወሰዱ ሁለት ተጨማሪ ሰዎች...