በብራዚል ውርጃን የሚያግደውን ረቂቅ ሕግ በመቃወም ሰልፍ ተደረገ
በብራዚል ውርጃን ወንጀል የሚያደርገውን የሕግ ረቂቅ በመቃወም በርካቶች ኮፓካባና የባሕር ዳርቻ ትላንት እሁድ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል።
በረቂቅ ሕጉ መሠረት 22 ሳምንትና ከዛም በላይ የሆነውን ጽንስ ማስወረድ እንደ ነፍስ ማጥፋት ተቆጥሮ እስከ 20 ዓመታት የሚደርስ የእስር ቅጣት ያስከትላል።
አሁን ባለው ሕግ በብራዚል ውርጃ መፈጸም ከአንድ እስከ ሶስት ዓመታት በእስር ያስቀጣል።
በአስገድዶ መደፈር ወይም እርግዝናው ለእናቲቱ ሕይወት አስጊ ከሆነ ግን ውርጃ...