አንድ የእስራኤል ዜጋ በዌስት ባንክ ተተኩሶበት ሞተ
ግጭት እየተስፋፋባት ባለው የፍልስጤም ግዛት በሆነችው በሰሜን ዌስት ባንክ፤ በዛሬ ዕለት አንድ የእስራኤል ዜጋ ተተኩሶበት ሞቶ መገኘቱን የእስራኤል ወታደራዊ ኃይል አስታውቋል። ቃልቂሊያ በተሰኘችው እና የእስራኤል ሰራዊቶች በሚንቀሳቀሱባት ከተማ ሟቹ መገኘቱን ተገልጿል። መግለጫው በዛሬው ዕለት በዌስት ባንክ ሁለት ታጣቂዎች በእስራኤል ኃይሎች ከተገደሉ በኋላ ነው የወጣው።
ይሁን እንጂ ምንም ዓይነት ተጨማሪ መረጃ ለህዝብ ይፋ አልተደረገም።
የእስራኤል እና ሃማስ...