በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ቡድኖች ላይ የሚፈፀመው አፈና እንዲቆም ተጠየቀ
የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሀገር ውስጥ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማት እና የሲቪክ ማህበራት ላይ የሚፈፅሙትንና እየተባባሰ የሄደውን አፈና በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አምስት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ።
አፈናው በአካል እና በዲጂታል የሚደረግ ክትትልን፣ የቃል ትንኮሳን፣ ማስፈራራትን እና ዛቻዎችን እንደሚያካትት የገለጹት ተቋማቱ፣ እነዚህ ድርጊቶች የሰብዓዊ መብት ተቋማት በሀገሪቱ ውስጥ ሰብዓዊ መብቶችን የማስከበር እና ሲጣሱ ደግሞ...