• 0 Comments 1 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • Haileleul Aph, የተባለው ልጅ ቼ በለውን እንዲህ ይበለጥጠዋል፡፡
    
    -
    ብሎክ ከተደራረግከው ሰው ጋራ እንዲህ ያለ ቀና ስብዕናን መመልከት ሰውየውን እንድታከብረው ያደርግሃል፡፡
    -
    ቼ በለው - Che Belew የሚሏት ገጽ በተከፈተች በሳምንቷ ስድስት ሺ ሰው ላይክ ብሏታል፡፡ ተከተላት፡፡ አሪፍ ነገር ታኝባታለህ፡፡
    -
    (አሸወይና ቀን ይስጥህ ጌታዬ!)
    -
    -
    -
    -
    -
    -
    እናም ኢትዮጲያዊ ይህን የመሰለ መፅሃፍ ሳያነብ ሃምሳ አመት ይሞላውና ይሞታል፡፡
    .
    አንዳንድ መፅሃፍ አለ….ሰላሳ ጊዜ ልታነበው ታግለህ ከአምስት ገፅ በላይ የማትሄደው……ብትሄደውም አቅለሽልሾ የሚያስመልስህ፡፡ አንዳንድ መፅሃፍ አለ መግቢያውን ማንበብ እንደጀመርክ ሳታስበው ራስህን የመጨረሻው ገፅ ላይ የምታገኝበት፡፡ በማለቁ የምትናደድበት፥ ካነበብከው በኋላ በገፆቹ ብዛት ልክ ህይወትህ ላይ ጣዕም የሚጨምር፡፡
    .
    ይህ መፅሃፍ 179 ገፆችና የኛኑ ዘመን ቀደዳዎችና ወሬዎች እንደወረደ ያስቀመጡ 19 ክፍሎች አሉት፡፡ ቀደዳዎቹ በዋነኛነት የእኛው ፖለቲካ፥ ማህበራዊ፥ ኢኮኖሚ፥ ታሪክ፥ ስነልቦና እና ሌሎችም የሰፈር አሉባልታዎች መልኮቻችን ላይ ያተኩራሉ፡፡ በእያንዳንዱ ትንተናም እኛኑ የሚያስቃኙ፥ የሚተቹ፥ የሚያላግጡ፥ የሚያመሰግኑ ሀተታዎች ተቀምጠዋል፡፡ እድልህ ሆኖ መፅሃፉ እጅህ ከገባ ከመግቢያው ጀምረህ ትታዘባለህ፡፡ እየታዘብክ ትስቃለህ፥ ትገረማለህ፥ ትናደዳለህ፡፡ ልክ ልክህን የሚነግርህን፥ የለመድከውንና አሜን ያልከውን የሚቃረንብህን ሃሳብ የምትችልበት ትዕግስቱ ካለህ እየተዝናናህ ትማርበታለህ፡፡
    .
    ሀ. ልጆቼን ላሳድግበት
    የያ ትውልድ ትራፊዎችና የዚህ ትውልድ አባቶች ለምን ፍርሃት እንደተጫናቸው ከመጀመሪያዎቹ ገፆች ጀምሮ ብዙዎቹ ተረኮች ላይ ታገኛለህ፡፡ ሁሉም የኖሩትን ቢኖሩም፥ የሚያውቁትን ቢያውቁም…መጨረሻቸውን ለማሳመር እኛን ለማሳደግ አንገት መድፋት እንደመረጡ ትገነዘባለህ፡፡
    “ለልጅ ማሳደግ ሲል ፖለቲካን እርግፍ አድርጎ የተወ” (ገ.41) እየተባለ የሚቀደድለት ሰው ታገኛለህ፡፡
    እንዲህ አይነት ፈሪ አባቶች ምን አይነት ልጆች እንደሚያፈሩ ምንም ያለው ነገር ባይኖርም፡፡
    .
    ለ. ነፋስ አመጣሽ ባለሃብቶች
    በከተማው ድንገት ዱብ የሚሉ ጀማሪ ባለሃብቶች ከየት ተነስተው፥ በየት በኩል አሳብረው የት እንደደረሱ ይተርክልሃል፡፡ ሁሉንም አካሄዳቸው ያመሳስላቸዋል፡፡ ከነማን ጋር ተመሳጥረው ምን ሰሩ የሚለው የከተማ ጭምጭምታ ይበልጥ ግዘፍ ነስቶ እና በትልቁ የተዘረጋ መዋቅር ሆኖ ይሳልልሃል፡፡
    በአቋራጭ መክበር ምን እንደሆነ ታውቃለህ? በአጭር ጊዜ እንዴት ቱጃር መሆን እንደሚቻል ማወቅ ትፈልጋለህ? የአቡሽ አያሌውን አስራ አምስቱ የሃብት መንገዶች የሚለውን መፅሃፍ ወርውርና ይህንን መፅሃፍ አንብብ፡፡ “ታግሎ ታግሎ ድህነቱን ያሸነፈና ኢንቨስተር የሆነ” ሰው ታሪክ ጥሩ ሞቲቬሽን ይሆንሃል፡፡ አየር ባየር ንግድ 101ም ይሰጥሃል፡፡
    “በቀደም እንዳለፈለት ያስታውቃል፡፡ የሚይዘው መኪናና ወዙ አይገናኙም” ብሎ ሙድ ቢይዝብህ ነው እንጂ፡፡ (ገ.27)
    ሃብታም ከሆንክ በኋላ ኑሮዬ እንዴት ይሆናል ብለህም እንዳትሰጋ፡፡
    “እንደው ይበለውና ከየት እንዴት በየት የሚለውን ጥያቄ ባላየ አልፈነው - እኛ ሃገር ውስጥ አንዱ ነፋስ አመጣሽ ሠገጤ ከትቢያ ተነስቶ በብርሃን ፍጥነት እልፍአእላፍ ሚለየን ብሮችን ቢያፍስ ምን ይሆናል?” (ገ.89)
    .
    ከዚህ ባሻገር ገበያውን ብቻ ሳይሆን እንስቶቻችንን እንዴት እንደተቆጣጠሩ፥ ቤተሰባዊ አኗኗራቸው ምን እንደሚመስል ይተረክልሃል፡፡
    እስከ መኝታ ቤት ገመናው ድረስ፡፡ እግረ መንገድም እንዴት ለሃብታሞቻችን አጨብጫቢዎች እንደሆንን አስታኮ ሸንቁጦህ ያልፋል፡፡
    .
    ሐ. ዝቅተኛ ገቢ ስላላቸው ሰዎች
    የደሃስ ኑሮ ሲቀደድ ምን ይመስላል? በቂ መልስ አለልህ፡፡ የልመናን ስነልቦና ሳይቀር ተመልክቶ እያመሰጠረ፡፡ ከቤት ሰራተኞቻችን እስከ አውቶቡስ ተጠቃሚዎቻችን የኑሮ ገፅታ ማብራሪያ ይሰጥሃል፡፡ አመትባልን አስታኮ በድህነትህ ላይ ቀልድ ይቀልዳል፡፡
    “ዶሮ፣ ቅቤ፣ ሽንኩርትና በግ ዋጋቸው ስለናረ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች በዓሉን ለማክበር መቸገራቸውን አንዳንድ ኗሪዎች እንዴት እንደ ገለፁ አይነት፤ አዝግ የሆነ የቀደዳ መስመር አላስይዝህም፡፡…….ያዲሳባ ድሃ አይደለም በዓሉን፣ የሰርክ ኑሮውን እንዴት አብቃቅቶ እንደሚኖር ሚስጥሩን ተክልዬም አልደረሱበትም፡፡” (ገ.65)
    .
    መ. ፌሚኒዝምን አፈር ማስበላት
    በዚህ መፅሃፍ እንደ አክራሪ ፌሚኒዝም በአራት ቁጥር ምት አገጩን የተባለ አስተሳሰብ ማግኘት ከባድ ነው፡፡ ምናልባት ደራሲው እንደሚታማው ብዙጊዜውን ሴቶች ላይ ስለሚያባክን ይሆናል፡፡ ባንድ ጠበቃ በጀነጀነበት ተረኩ ሴቷን እንዲህ ይላታል፡፡
    “ለሴት መብት ተቆርቋሪ፣ ተከራካሪ፣ ተመራማሪ፣ ተንጨርጫሪ፣ ፍሪክ ነኝ አይነት ጭውቴዎች አሏት” (ገ .51)
    በመፅኃፉ ውስጥ ሴት ቡና ማፍላቷ ጭቆና ነው ብላ ከምታስብ ሴት ጀምሮ እስከ በጊዜ ሂደት ወንድ ጠል ስለሆነች ሴት ይቀደዳል፡፡ ለቁምነገር ወሬ እንጂ ለሚስትነት አይሆኑም እስከሚለው ድረስ፡፡
    ገፅ157 ላይ ደሞ ይሄ አለልህ፡፡
    “ክርር ያለች ፌሚኒስት ሴትዮ አግብተህ ማታ ማታ ስለ ሰብዓዊ መብት አያያዝ ግድፈቶች፣ ስለሶርያ፣ ስለዶናልድ ትረምፕ፣ ዴሞክራሲ ስትከራከር አይሸክክህም? ሴትማ የሚያምርባት ውሃ ጠፋ፣ መብራት ጠፋ፣ አብሲቱ ተበላሸ፣ የቂቤ ዋጋ ጨመረ፣ የሚያምር ጫማ አይቼ ምናምን ስትል ነው….ሴትማ የሚያምርባት…”….እያለ ይቀጥላል፡፡
    .
    ሠ. አዳዲስ ትርጎሞችን ስለማምጣት፡፡
    እንዳልኩህ እዚህ መፅሃፍ ላይ ብዙ ነገር ፈርሶ ሲሰራ ታያለህ፡፡ ብዙ ሃሳብ ሲብላላ ከስሩ ሲፈርስ እንደገና ሲገነባ ትመለከታለህ፡፡ ከተመቸህ ታደንቀዋለህ፡፡ ካልተመቸህም ታደንቀዋህ፥ እየተናደድክበት፡፡ እስቲ ይሄን የብሄር ዴፊኒሽን እየውማ፡፡
    “ ብሔር- የላባደሩ መጫወቻ ካርድ ከተባነነበት በኋላ ማንነት በሚል ሽፋን የተፈጠረ አዲስ መጫወቻ ጆከር፡፡ አንድ ሰው ልክ ሲያልፍለት እና ሲሞላለት የሚሸሸው አልያም use and abuse የሚያደርገው ማስክ፡፡ ከከተሜነት ጋራ የመደብ ቅራኔ የፈጠረ፣ በባህሪው ሰገጤያዊ፣ እየከሰመ የሚሄድ፣ የተባነነበት፣ የተበላ እቁብ፡፡” (ገ.155)
    .
    ረ. አካፋን አካፋ
    መፅሃፉን ስታነብ ፀሃፊውን የሚጠሉት ሰዎች ምን እንደዚያ እንደሚያስጮሃቸው ትረዳለህ፡፡ ሲነግርህ ለነገ አይልም፡፡ ዲያስፖራውን ጠሽ ወይም የዞረበት ሲል ይጠራዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ፥ ሆዳም ሚዲያዎች፥ የከሸፈው ትውልድ፥ ገዢው ፓርቲ፥ ብር አግበስባሽ ኤንጂኦዎች፥ ቤተክህነት፥ የቸርች ኳየሮች እና ፓስተሮቻቸው……ሁሉንም በምክንያታዊ ጠረባ ሲዘርራቸው ትመለከታለህ፡፡
    ፀረ ሙስናም ከቴራ አልተረፈም፡፡
    “ባለፈው አንዱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ስለሙስና አስከፊነት ህዝቡን የሚያስተምር ማስታወቂያ ለማሰራት ጨረታ አውጥቶ፣ ከክፍያው ላይ ሃያ በመቶውን ለዋናዎቹ በጎቦ መልክ እለቃለሁ ያለው ድርጅት አሸነፈ..በብሎ ያወራኝ ለታ ነው ምፅኣት እንደቀረበ እርግጠኛ የሆንኩት፡፡ “ (ገ.53)
    በገፅ 31 ላይ አፍሪካንና የአፍሪካን ቀንድ፥ ቀንዱን ሲለው ራስህን አሞህ ካልተኛህ ባንዳ ነህ ማለት ነው፡፡ ይሄ እርጉም አህጉር- ይሄ ከይሲ ጥቁር ህዝብ- ይሄ ችጋር የሚበጠብጠው የአፍሪቃ ቀንድ- ይሄ ጦርነት የማያጣው ቀንዳ ክፍለ አህጉር- ይሄ ደዌና ቸነፈር ያቀረጨጨው ጊንጥ ህዝብ - በዘር በክልል በድንበር የተከፋፈለ- ሊባላ ከጫፍ የደረሰ- ድሮም አሁንም ወደፊትም ራሱን ችሎ በልቶ ለማደር የማይችል አፍሪቃዊ!..... እውነትም The hopeless continent.
    .
    ሸ. ከራስ ሲቀዳ
    ቼበለው ከልጅነት ታሪክ እስከ የጉዞ ገጠመኝ፥ ከከተማ አሉባልታ እስከ የዘመድ አዝማድ ሰርግ እየተቀመመ የተፃፈ መፅሃፍ ነው፡፡ ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት እስከ ኦሩሙማ፥ ከትግራዋይ ላዕላይነት እስከ ስራ ገጠመኞች ተካተውበታል፡፡ የተጨቆኑ ሃሳቦችን ብቻም ሳይሆን ቢጫ ጀሪካንንም ከተናቀችበት ነፃ አውጥቷል፡፡ እንዴት አድርጎ የማበረሰቡ አኗኗር ውስጥ እንደሰረገ ከነአመጣጡ እያስረዳ ድንቅ ሲሞቦሊክ ኢንተራክሽኒስት ትንተናውን ያስቀምጥልሃል፡፡ በቀላል ቋንቋ የከተሜውን ድምፅ ይዞ እስከ የባህል ስነቃሎች ያጣቅስልሃል፡፡ ከአበረ አያሌው እስከ ገብረክርስቶስ ደስታ ግጥሞች ከወሬ ጋር ተሰናስለው ታገኛለህ፡፡ ከመልካም ዘይቤያዊ አጠቃቀም ጋር፡፡
    ቼ የሚለው የመጨረሻው ክፍል ቀደዳ በራሱ ሊትሬቸር ሪቪው በለው፡፡ በአስራ ዘጠኝ ገፆች ብቻ ሃያ ሶስት ማጣቀሻዎች ተፅፈውልሃል፡፡ ከቴዎድሮስ እስከ ኢሃዴግ፥ ከአድዋ ድል እስከ ኤርትራ ፌደሬሽን፥ ከልጅ እያሱ እስከ ደርግ…በእያንዳንዱ አገዛዝ የሆነውንና የተሰራውን ታያለህ፡፡ ከጥንት እስካሁን ከጦርነት እና ግጭት ለምን እንዳልወጣን እያሰብክ ትገረማለህ፡፡ መፅሃፉ በጠቅላላ በሚያነሳቸው ሂሶች ራስህንና ሀገርህን ትታዘባለህ፡፡ ተመፃዳቂነት፥ አድርባይነት፥ ራስወዳድነት፥ አስመሳይነት…….እንዴት እንደተጠናወተን ትመለከትና ታዝናለህ፡፡ በስተመጨረሻው በነቢይ መኮንን ግጥም ቢሆንም ቢሆንም ይቺ ናት ሃገርህ ብሎ እስኪሰናበትህ ድረስ፡፡ ምናልባት ቼ የምትለዋን ክፍል ብቻ በአምስት ሞቶ ገፆች ፅፏት እስኪመጣ ድረስ፡፡
    (ገፆቹን ጨርሰህ በውስጠኛው ሽፋን በኩል ሃርድ የጫረ በሬ አርማ ካየህ መፅሃፉን ቀድሞህ አንብቦት እንዳይሆን ስጋ፡፡)
    .
    ፍጠን ወንድማለም፡፡
    ቼበለው!!
    Haileleul Aph, የተባለው ልጅ ቼ በለውን እንዲህ ይበለጥጠዋል፡፡  - ብሎክ ከተደራረግከው ሰው ጋራ እንዲህ ያለ ቀና ስብዕናን መመልከት ሰውየውን እንድታከብረው ያደርግሃል፡፡ - ቼ በለው - Che Belew የሚሏት ገጽ በተከፈተች በሳምንቷ ስድስት ሺ ሰው ላይክ ብሏታል፡፡ ተከተላት፡፡ አሪፍ ነገር ታኝባታለህ፡፡ - (አሸወይና ቀን ይስጥህ ጌታዬ!) - - - - - - እናም ኢትዮጲያዊ ይህን የመሰለ መፅሃፍ ሳያነብ ሃምሳ አመት ይሞላውና ይሞታል፡፡ . አንዳንድ መፅሃፍ አለ….ሰላሳ ጊዜ ልታነበው ታግለህ ከአምስት ገፅ በላይ የማትሄደው……ብትሄደውም አቅለሽልሾ የሚያስመልስህ፡፡ አንዳንድ መፅሃፍ አለ መግቢያውን ማንበብ እንደጀመርክ ሳታስበው ራስህን የመጨረሻው ገፅ ላይ የምታገኝበት፡፡ በማለቁ የምትናደድበት፥ ካነበብከው በኋላ በገፆቹ ብዛት ልክ ህይወትህ ላይ ጣዕም የሚጨምር፡፡ . ይህ መፅሃፍ 179 ገፆችና የኛኑ ዘመን ቀደዳዎችና ወሬዎች እንደወረደ ያስቀመጡ 19 ክፍሎች አሉት፡፡ ቀደዳዎቹ በዋነኛነት የእኛው ፖለቲካ፥ ማህበራዊ፥ ኢኮኖሚ፥ ታሪክ፥ ስነልቦና እና ሌሎችም የሰፈር አሉባልታዎች መልኮቻችን ላይ ያተኩራሉ፡፡ በእያንዳንዱ ትንተናም እኛኑ የሚያስቃኙ፥ የሚተቹ፥ የሚያላግጡ፥ የሚያመሰግኑ ሀተታዎች ተቀምጠዋል፡፡ እድልህ ሆኖ መፅሃፉ እጅህ ከገባ ከመግቢያው ጀምረህ ትታዘባለህ፡፡ እየታዘብክ ትስቃለህ፥ ትገረማለህ፥ ትናደዳለህ፡፡ ልክ ልክህን የሚነግርህን፥ የለመድከውንና አሜን ያልከውን የሚቃረንብህን ሃሳብ የምትችልበት ትዕግስቱ ካለህ እየተዝናናህ ትማርበታለህ፡፡ . ሀ. ልጆቼን ላሳድግበት የያ ትውልድ ትራፊዎችና የዚህ ትውልድ አባቶች ለምን ፍርሃት እንደተጫናቸው ከመጀመሪያዎቹ ገፆች ጀምሮ ብዙዎቹ ተረኮች ላይ ታገኛለህ፡፡ ሁሉም የኖሩትን ቢኖሩም፥ የሚያውቁትን ቢያውቁም…መጨረሻቸውን ለማሳመር እኛን ለማሳደግ አንገት መድፋት እንደመረጡ ትገነዘባለህ፡፡ “ለልጅ ማሳደግ ሲል ፖለቲካን እርግፍ አድርጎ የተወ” (ገ.41) እየተባለ የሚቀደድለት ሰው ታገኛለህ፡፡ እንዲህ አይነት ፈሪ አባቶች ምን አይነት ልጆች እንደሚያፈሩ ምንም ያለው ነገር ባይኖርም፡፡ . ለ. ነፋስ አመጣሽ ባለሃብቶች በከተማው ድንገት ዱብ የሚሉ ጀማሪ ባለሃብቶች ከየት ተነስተው፥ በየት በኩል አሳብረው የት እንደደረሱ ይተርክልሃል፡፡ ሁሉንም አካሄዳቸው ያመሳስላቸዋል፡፡ ከነማን ጋር ተመሳጥረው ምን ሰሩ የሚለው የከተማ ጭምጭምታ ይበልጥ ግዘፍ ነስቶ እና በትልቁ የተዘረጋ መዋቅር ሆኖ ይሳልልሃል፡፡ በአቋራጭ መክበር ምን እንደሆነ ታውቃለህ? በአጭር ጊዜ እንዴት ቱጃር መሆን እንደሚቻል ማወቅ ትፈልጋለህ? የአቡሽ አያሌውን አስራ አምስቱ የሃብት መንገዶች የሚለውን መፅሃፍ ወርውርና ይህንን መፅሃፍ አንብብ፡፡ “ታግሎ ታግሎ ድህነቱን ያሸነፈና ኢንቨስተር የሆነ” ሰው ታሪክ ጥሩ ሞቲቬሽን ይሆንሃል፡፡ አየር ባየር ንግድ 101ም ይሰጥሃል፡፡ “በቀደም እንዳለፈለት ያስታውቃል፡፡ የሚይዘው መኪናና ወዙ አይገናኙም” ብሎ ሙድ ቢይዝብህ ነው እንጂ፡፡ (ገ.27) ሃብታም ከሆንክ በኋላ ኑሮዬ እንዴት ይሆናል ብለህም እንዳትሰጋ፡፡ “እንደው ይበለውና ከየት እንዴት በየት የሚለውን ጥያቄ ባላየ አልፈነው - እኛ ሃገር ውስጥ አንዱ ነፋስ አመጣሽ ሠገጤ ከትቢያ ተነስቶ በብርሃን ፍጥነት እልፍአእላፍ ሚለየን ብሮችን ቢያፍስ ምን ይሆናል?” (ገ.89) . ከዚህ ባሻገር ገበያውን ብቻ ሳይሆን እንስቶቻችንን እንዴት እንደተቆጣጠሩ፥ ቤተሰባዊ አኗኗራቸው ምን እንደሚመስል ይተረክልሃል፡፡ እስከ መኝታ ቤት ገመናው ድረስ፡፡ እግረ መንገድም እንዴት ለሃብታሞቻችን አጨብጫቢዎች እንደሆንን አስታኮ ሸንቁጦህ ያልፋል፡፡ . ሐ. ዝቅተኛ ገቢ ስላላቸው ሰዎች የደሃስ ኑሮ ሲቀደድ ምን ይመስላል? በቂ መልስ አለልህ፡፡ የልመናን ስነልቦና ሳይቀር ተመልክቶ እያመሰጠረ፡፡ ከቤት ሰራተኞቻችን እስከ አውቶቡስ ተጠቃሚዎቻችን የኑሮ ገፅታ ማብራሪያ ይሰጥሃል፡፡ አመትባልን አስታኮ በድህነትህ ላይ ቀልድ ይቀልዳል፡፡ “ዶሮ፣ ቅቤ፣ ሽንኩርትና በግ ዋጋቸው ስለናረ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች በዓሉን ለማክበር መቸገራቸውን አንዳንድ ኗሪዎች እንዴት እንደ ገለፁ አይነት፤ አዝግ የሆነ የቀደዳ መስመር አላስይዝህም፡፡…….ያዲሳባ ድሃ አይደለም በዓሉን፣ የሰርክ ኑሮውን እንዴት አብቃቅቶ እንደሚኖር ሚስጥሩን ተክልዬም አልደረሱበትም፡፡” (ገ.65) . መ. ፌሚኒዝምን አፈር ማስበላት በዚህ መፅሃፍ እንደ አክራሪ ፌሚኒዝም በአራት ቁጥር ምት አገጩን የተባለ አስተሳሰብ ማግኘት ከባድ ነው፡፡ ምናልባት ደራሲው እንደሚታማው ብዙጊዜውን ሴቶች ላይ ስለሚያባክን ይሆናል፡፡ ባንድ ጠበቃ በጀነጀነበት ተረኩ ሴቷን እንዲህ ይላታል፡፡ “ለሴት መብት ተቆርቋሪ፣ ተከራካሪ፣ ተመራማሪ፣ ተንጨርጫሪ፣ ፍሪክ ነኝ አይነት ጭውቴዎች አሏት” (ገ .51) በመፅኃፉ ውስጥ ሴት ቡና ማፍላቷ ጭቆና ነው ብላ ከምታስብ ሴት ጀምሮ እስከ በጊዜ ሂደት ወንድ ጠል ስለሆነች ሴት ይቀደዳል፡፡ ለቁምነገር ወሬ እንጂ ለሚስትነት አይሆኑም እስከሚለው ድረስ፡፡ ገፅ157 ላይ ደሞ ይሄ አለልህ፡፡ “ክርር ያለች ፌሚኒስት ሴትዮ አግብተህ ማታ ማታ ስለ ሰብዓዊ መብት አያያዝ ግድፈቶች፣ ስለሶርያ፣ ስለዶናልድ ትረምፕ፣ ዴሞክራሲ ስትከራከር አይሸክክህም? ሴትማ የሚያምርባት ውሃ ጠፋ፣ መብራት ጠፋ፣ አብሲቱ ተበላሸ፣ የቂቤ ዋጋ ጨመረ፣ የሚያምር ጫማ አይቼ ምናምን ስትል ነው….ሴትማ የሚያምርባት…”….እያለ ይቀጥላል፡፡ . ሠ. አዳዲስ ትርጎሞችን ስለማምጣት፡፡ እንዳልኩህ እዚህ መፅሃፍ ላይ ብዙ ነገር ፈርሶ ሲሰራ ታያለህ፡፡ ብዙ ሃሳብ ሲብላላ ከስሩ ሲፈርስ እንደገና ሲገነባ ትመለከታለህ፡፡ ከተመቸህ ታደንቀዋለህ፡፡ ካልተመቸህም ታደንቀዋህ፥ እየተናደድክበት፡፡ እስቲ ይሄን የብሄር ዴፊኒሽን እየውማ፡፡ “ ብሔር- የላባደሩ መጫወቻ ካርድ ከተባነነበት በኋላ ማንነት በሚል ሽፋን የተፈጠረ አዲስ መጫወቻ ጆከር፡፡ አንድ ሰው ልክ ሲያልፍለት እና ሲሞላለት የሚሸሸው አልያም use and abuse የሚያደርገው ማስክ፡፡ ከከተሜነት ጋራ የመደብ ቅራኔ የፈጠረ፣ በባህሪው ሰገጤያዊ፣ እየከሰመ የሚሄድ፣ የተባነነበት፣ የተበላ እቁብ፡፡” (ገ.155) . ረ. አካፋን አካፋ መፅሃፉን ስታነብ ፀሃፊውን የሚጠሉት ሰዎች ምን እንደዚያ እንደሚያስጮሃቸው ትረዳለህ፡፡ ሲነግርህ ለነገ አይልም፡፡ ዲያስፖራውን ጠሽ ወይም የዞረበት ሲል ይጠራዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ፥ ሆዳም ሚዲያዎች፥ የከሸፈው ትውልድ፥ ገዢው ፓርቲ፥ ብር አግበስባሽ ኤንጂኦዎች፥ ቤተክህነት፥ የቸርች ኳየሮች እና ፓስተሮቻቸው……ሁሉንም በምክንያታዊ ጠረባ ሲዘርራቸው ትመለከታለህ፡፡ ፀረ ሙስናም ከቴራ አልተረፈም፡፡ “ባለፈው አንዱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ስለሙስና አስከፊነት ህዝቡን የሚያስተምር ማስታወቂያ ለማሰራት ጨረታ አውጥቶ፣ ከክፍያው ላይ ሃያ በመቶውን ለዋናዎቹ በጎቦ መልክ እለቃለሁ ያለው ድርጅት አሸነፈ..በብሎ ያወራኝ ለታ ነው ምፅኣት እንደቀረበ እርግጠኛ የሆንኩት፡፡ “ (ገ.53) በገፅ 31 ላይ አፍሪካንና የአፍሪካን ቀንድ፥ ቀንዱን ሲለው ራስህን አሞህ ካልተኛህ ባንዳ ነህ ማለት ነው፡፡ ይሄ እርጉም አህጉር- ይሄ ከይሲ ጥቁር ህዝብ- ይሄ ችጋር የሚበጠብጠው የአፍሪቃ ቀንድ- ይሄ ጦርነት የማያጣው ቀንዳ ክፍለ አህጉር- ይሄ ደዌና ቸነፈር ያቀረጨጨው ጊንጥ ህዝብ - በዘር በክልል በድንበር የተከፋፈለ- ሊባላ ከጫፍ የደረሰ- ድሮም አሁንም ወደፊትም ራሱን ችሎ በልቶ ለማደር የማይችል አፍሪቃዊ!..... እውነትም The hopeless continent. . ሸ. ከራስ ሲቀዳ ቼበለው ከልጅነት ታሪክ እስከ የጉዞ ገጠመኝ፥ ከከተማ አሉባልታ እስከ የዘመድ አዝማድ ሰርግ እየተቀመመ የተፃፈ መፅሃፍ ነው፡፡ ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት እስከ ኦሩሙማ፥ ከትግራዋይ ላዕላይነት እስከ ስራ ገጠመኞች ተካተውበታል፡፡ የተጨቆኑ ሃሳቦችን ብቻም ሳይሆን ቢጫ ጀሪካንንም ከተናቀችበት ነፃ አውጥቷል፡፡ እንዴት አድርጎ የማበረሰቡ አኗኗር ውስጥ እንደሰረገ ከነአመጣጡ እያስረዳ ድንቅ ሲሞቦሊክ ኢንተራክሽኒስት ትንተናውን ያስቀምጥልሃል፡፡ በቀላል ቋንቋ የከተሜውን ድምፅ ይዞ እስከ የባህል ስነቃሎች ያጣቅስልሃል፡፡ ከአበረ አያሌው እስከ ገብረክርስቶስ ደስታ ግጥሞች ከወሬ ጋር ተሰናስለው ታገኛለህ፡፡ ከመልካም ዘይቤያዊ አጠቃቀም ጋር፡፡ ቼ የሚለው የመጨረሻው ክፍል ቀደዳ በራሱ ሊትሬቸር ሪቪው በለው፡፡ በአስራ ዘጠኝ ገፆች ብቻ ሃያ ሶስት ማጣቀሻዎች ተፅፈውልሃል፡፡ ከቴዎድሮስ እስከ ኢሃዴግ፥ ከአድዋ ድል እስከ ኤርትራ ፌደሬሽን፥ ከልጅ እያሱ እስከ ደርግ…በእያንዳንዱ አገዛዝ የሆነውንና የተሰራውን ታያለህ፡፡ ከጥንት እስካሁን ከጦርነት እና ግጭት ለምን እንዳልወጣን እያሰብክ ትገረማለህ፡፡ መፅሃፉ በጠቅላላ በሚያነሳቸው ሂሶች ራስህንና ሀገርህን ትታዘባለህ፡፡ ተመፃዳቂነት፥ አድርባይነት፥ ራስወዳድነት፥ አስመሳይነት…….እንዴት እንደተጠናወተን ትመለከትና ታዝናለህ፡፡ በስተመጨረሻው በነቢይ መኮንን ግጥም ቢሆንም ቢሆንም ይቺ ናት ሃገርህ ብሎ እስኪሰናበትህ ድረስ፡፡ ምናልባት ቼ የምትለዋን ክፍል ብቻ በአምስት ሞቶ ገፆች ፅፏት እስኪመጣ ድረስ፡፡ (ገፆቹን ጨርሰህ በውስጠኛው ሽፋን በኩል ሃርድ የጫረ በሬ አርማ ካየህ መፅሃፉን ቀድሞህ አንብቦት እንዳይሆን ስጋ፡፡) . ፍጠን ወንድማለም፡፡ ቼበለው!!
    0 Comments 0 Shares
  • የተቀነጨበውን አንብበው እስኪ
    • • • • •
    ". . . መቼም ዋናው ፍቅር ነው እንዳትለኝ! ሃ ሃ ሃ ተው አታስቀኝ! ጀለሴ የፍቅር concept ሰመመን መጽሃፍ ላይ Save ተደርጎልሃል፤ ሂድና አንብበው፤ ያውም ካገኘኸው፡፡ . . . የድሮ ሰው ፍቅር ይይዘው ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ሰው የፍቅር ደብዳቤ ይጽፍ ነበር አሉ፡፡ የደጉ ዘመን ሰው አፈቀርኩ ብሎ ይከሳ ይመነምን ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ወጣት ፎንቃ ጠልፎት የአስቴር አወቀን ካሴት እያዳመጠ ስቅስቅ ብሎ ያለቅስ ነበር አሉ፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . ባል፣ ጓደኛ፣ መልክ፣ ወጣትነት፣ ፈገግታ፣ ወግ፣ አመል፣ Femininity፣ ደስታ፣ ፍቅር፣ ሰላም፣ ፈላጊ፣ ለካፊ፣ አሽኮርማሚ፣ ሞካሪ፣ አፍቃሪ ካጡ፤ ተናዳፊ ጊንጥ የመሰሉ ብስጩ ፌሚኒስቶች ጋራ ገጠመች፡፡ የግሩፓቸው አባል ሆነች፡፡ ወንድ የባሰ ጠላች!"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . የዘውድ አገዛዝ፤ የደርግ ፋሺዝም፣ መደራጀት፣ ዴሞክራሲያ፣ መሥዋዕትነት፣ጆሊ-ጃኪዝም፣ ትጥቅ ትግል፣ ስር-ነቀል ለውጥ፣ ላብ አደር፣ ኢምፔሪያሊዝም፣ መሣፍንታዊው ስርዐት፣ ጭሰኛ፣ ንቅናቄ፣ ሠፊው ሕዝብ፣ ቅራኔ፣ ሃይሌ ፊዳ፣ መደብ፣ ዴሞክራሲያ፣ እድገት በኀብረት፣ መኢሶን፣ ሰርጎ-ገብ፣ አፈና፣ ነጭ ሽብር. . . የሚሉ ቃላቶችና ሃረጎች አእምሮው ላይ የሚመላለሱበት ጎረምሳ ዓይን፡፡ በህቡዕ የተደራጀ፣ በሴል የተዋቀረ፣ በህቡዕ በራሪ-ወረቀት የበተነ፣ የከለላ ሽፋን የሰጠ፤ ምናልባትም ከሴሉ አመራር በወረደለት ትዕዛዝ መሰረት በፋሺስቱ ስርዓት አገልጋዮች ላይ የግድያ እርምጃን የፈጸመ ቆራጥ አብዮታዊ ወጣት ዓይን፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . ደሞዝ የማይበቃቸው፤ ኑሮ ያካለባቸው አራት የኢቲቪና የአዲስ ዘመን ጋዜጠኞች ዳጎስ ያለ ውሎ አበል ተከፍሏቸው ይመጡና ነገርየውን እንደ ትልቅ ልማታዊ ዜና አካብደው ይዘግቡታል፡፡ መጨረሻ ላይ 47 ገጽ የሚሞላው Evaluation Report በExternal Consultant ተረቅቆ፤ “በዚህ ቦኖ መሰራት ሳቢያ ሆዱን የሚያመው አበሻ በ16% ቀነሰ፤ ሴቶች ታጥበው ቀሉ፤ ወደ ጅረት ወርደው ውሃ የሚቀዱበት ሰዓት ስላጠረላቸው ጤና ጣብያ ሄደው መውለድ ጀመሩ፤ ህጻናት ወፈሩ፤ Climate Changeን ለመከላከል በተዘዋዋሪ ተጽእኖ ፈጠረ . . .”ምናምን የሚል ጆካ ሪፖርት ተጽፎ፤ ሴቶችና ህጻናት ውሃ ጠጥተው ፈገግ ሲሉ የተነሱት ፎቶ ተጨምሮበት ለፈረንጅ ይላካል፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    ". . . ህምም . . . ‘እሺ አይለውም’"
    የተቀነጨበውን አንብበው እስኪ • • • • • ". . . መቼም ዋናው ፍቅር ነው እንዳትለኝ! ሃ ሃ ሃ ተው አታስቀኝ! ጀለሴ የፍቅር concept ሰመመን መጽሃፍ ላይ Save ተደርጎልሃል፤ ሂድና አንብበው፤ ያውም ካገኘኸው፡፡ . . . የድሮ ሰው ፍቅር ይይዘው ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ሰው የፍቅር ደብዳቤ ይጽፍ ነበር አሉ፡፡ የደጉ ዘመን ሰው አፈቀርኩ ብሎ ይከሳ ይመነምን ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ወጣት ፎንቃ ጠልፎት የአስቴር አወቀን ካሴት እያዳመጠ ስቅስቅ ብሎ ያለቅስ ነበር አሉ፡፡" ✿ ✿ ✿ " . . . ባል፣ ጓደኛ፣ መልክ፣ ወጣትነት፣ ፈገግታ፣ ወግ፣ አመል፣ Femininity፣ ደስታ፣ ፍቅር፣ ሰላም፣ ፈላጊ፣ ለካፊ፣ አሽኮርማሚ፣ ሞካሪ፣ አፍቃሪ ካጡ፤ ተናዳፊ ጊንጥ የመሰሉ ብስጩ ፌሚኒስቶች ጋራ ገጠመች፡፡ የግሩፓቸው አባል ሆነች፡፡ ወንድ የባሰ ጠላች!" ✿ ✿ ✿ " . . . የዘውድ አገዛዝ፤ የደርግ ፋሺዝም፣ መደራጀት፣ ዴሞክራሲያ፣ መሥዋዕትነት፣ጆሊ-ጃኪዝም፣ ትጥቅ ትግል፣ ስር-ነቀል ለውጥ፣ ላብ አደር፣ ኢምፔሪያሊዝም፣ መሣፍንታዊው ስርዐት፣ ጭሰኛ፣ ንቅናቄ፣ ሠፊው ሕዝብ፣ ቅራኔ፣ ሃይሌ ፊዳ፣ መደብ፣ ዴሞክራሲያ፣ እድገት በኀብረት፣ መኢሶን፣ ሰርጎ-ገብ፣ አፈና፣ ነጭ ሽብር. . . የሚሉ ቃላቶችና ሃረጎች አእምሮው ላይ የሚመላለሱበት ጎረምሳ ዓይን፡፡ በህቡዕ የተደራጀ፣ በሴል የተዋቀረ፣ በህቡዕ በራሪ-ወረቀት የበተነ፣ የከለላ ሽፋን የሰጠ፤ ምናልባትም ከሴሉ አመራር በወረደለት ትዕዛዝ መሰረት በፋሺስቱ ስርዓት አገልጋዮች ላይ የግድያ እርምጃን የፈጸመ ቆራጥ አብዮታዊ ወጣት ዓይን፡፡" ✿ ✿ ✿ " . . . ደሞዝ የማይበቃቸው፤ ኑሮ ያካለባቸው አራት የኢቲቪና የአዲስ ዘመን ጋዜጠኞች ዳጎስ ያለ ውሎ አበል ተከፍሏቸው ይመጡና ነገርየውን እንደ ትልቅ ልማታዊ ዜና አካብደው ይዘግቡታል፡፡ መጨረሻ ላይ 47 ገጽ የሚሞላው Evaluation Report በExternal Consultant ተረቅቆ፤ “በዚህ ቦኖ መሰራት ሳቢያ ሆዱን የሚያመው አበሻ በ16% ቀነሰ፤ ሴቶች ታጥበው ቀሉ፤ ወደ ጅረት ወርደው ውሃ የሚቀዱበት ሰዓት ስላጠረላቸው ጤና ጣብያ ሄደው መውለድ ጀመሩ፤ ህጻናት ወፈሩ፤ Climate Changeን ለመከላከል በተዘዋዋሪ ተጽእኖ ፈጠረ . . .”ምናምን የሚል ጆካ ሪፖርት ተጽፎ፤ ሴቶችና ህጻናት ውሃ ጠጥተው ፈገግ ሲሉ የተነሱት ፎቶ ተጨምሮበት ለፈረንጅ ይላካል፡፡" ✿ ✿ ✿ ". . . ህምም . . . ‘እሺ አይለውም’"
    Like
    1
    0 Comments 1 Shares
  • Like
    1
    1 Comments 0 Shares
  • የተቀነጨበውን አንብበው እስኪ
    • • • • •
    ". . . መቼም ዋናው ፍቅር ነው እንዳትለኝ! ሃ ሃ ሃ ተው አታስቀኝ! ጀለሴ የፍቅር concept ሰመመን መጽሃፍ ላይ Save ተደርጎልሃል፤ ሂድና አንብበው፤ ያውም ካገኘኸው፡፡ . . . የድሮ ሰው ፍቅር ይይዘው ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ሰው የፍቅር ደብዳቤ ይጽፍ ነበር አሉ፡፡ የደጉ ዘመን ሰው አፈቀርኩ ብሎ ይከሳ ይመነምን ነበር አሉ፡፡ የዱሮ ወጣት ፎንቃ ጠልፎት የአስቴር አወቀን ካሴት እያዳመጠ ስቅስቅ ብሎ ያለቅስ ነበር አሉ፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . ባል፣ ጓደኛ፣ መልክ፣ ወጣትነት፣ ፈገግታ፣ ወግ፣ አመል፣ Femininity፣ ደስታ፣ ፍቅር፣ ሰላም፣ ፈላጊ፣ ለካፊ፣ አሽኮርማሚ፣ ሞካሪ፣ አፍቃሪ ካጡ፤ ተናዳፊ ጊንጥ የመሰሉ ብስጩ ፌሚኒስቶች ጋራ ገጠመች፡፡ የግሩፓቸው አባል ሆነች፡፡ ወንድ የባሰ ጠላች!"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . የዘውድ አገዛዝ፤ የደርግ ፋሺዝም፣ መደራጀት፣ ዴሞክራሲያ፣ መሥዋዕትነት፣ጆሊ-ጃኪዝም፣ ትጥቅ ትግል፣ ስር-ነቀል ለውጥ፣ ላብ አደር፣ ኢምፔሪያሊዝም፣ መሣፍንታዊው ስርዐት፣ ጭሰኛ፣ ንቅናቄ፣ ሠፊው ሕዝብ፣ ቅራኔ፣ ሃይሌ ፊዳ፣ መደብ፣ ዴሞክራሲያ፣ እድገት በኀብረት፣ መኢሶን፣ ሰርጎ-ገብ፣ አፈና፣ ነጭ ሽብር. . . የሚሉ ቃላቶችና ሃረጎች አእምሮው ላይ የሚመላለሱበት ጎረምሳ ዓይን፡፡ በህቡዕ የተደራጀ፣ በሴል የተዋቀረ፣ በህቡዕ በራሪ-ወረቀት የበተነ፣ የከለላ ሽፋን የሰጠ፤ ምናልባትም ከሴሉ አመራር በወረደለት ትዕዛዝ መሰረት በፋሺስቱ ስርዓት አገልጋዮች ላይ የግድያ እርምጃን የፈጸመ ቆራጥ አብዮታዊ ወጣት ዓይን፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    " . . . ደሞዝ የማይበቃቸው፤ ኑሮ ያካለባቸው አራት የኢቲቪና የአዲስ ዘመን ጋዜጠኞች ዳጎስ ያለ ውሎ አበል ተከፍሏቸው ይመጡና ነገርየውን እንደ ትልቅ ልማታዊ ዜና አካብደው ይዘግቡታል፡፡ መጨረሻ ላይ 47 ገጽ የሚሞላው Evaluation Report በExternal Consultant ተረቅቆ፤ “በዚህ ቦኖ መሰራት ሳቢያ ሆዱን የሚያመው አበሻ በ16% ቀነሰ፤ ሴቶች ታጥበው ቀሉ፤ ወደ ጅረት ወርደው ውሃ የሚቀዱበት ሰዓት ስላጠረላቸው ጤና ጣብያ ሄደው መውለድ ጀመሩ፤ ህጻናት ወፈሩ፤ Climate Changeን ለመከላከል በተዘዋዋሪ ተጽእኖ ፈጠረ . . .”ምናምን የሚል ጆካ ሪፖርት ተጽፎ፤ ሴቶችና ህጻናት ውሃ ጠጥተው ፈገግ ሲሉ የተነሱት ፎቶ ተጨምሮበት ለፈረንጅ ይላካል፡፡"
    ✿ ✿ ✿
    ". . . ህምም . . . ‘እሺ አይለውም’"
    0 Comments 0 Shares
  • 1 Comments 0 Shares
  • 3 ጓደኛሞች አቤ,ከቤ እና አብቻ እሁድን ሀይቅ ዳር
    እየተዝናኑ ለማሳለፍ ይወስናሉ፡፡
    3ቱም የሚይዝቱን ነገር ይከፋፈላሉ አቤ, ምግብ ከቤ, የሚጠጣ ነገር "አብቻ" ደሞ ጫት ለመያዝ ይስማማሉ፡፡
    ሀይቅ ዳር በ1 ሰዓት ጉዞ ይደርሱና መናፈሻ ገብተው ምንጣፍ
    አንጥፈው ቁጭ አሉ፡፡ ሁሉም ያመጡትን እያወጡ ማስቀመጥ
    እንደጀመሩ "አብቻ" ጫቱን ገዝቶ እቤት እንዳስቀመጠውና
    ረስቶት እንደመጣ ይነግራቸዋል፡፡
    እዛ እንዳይገዙ ደሞ 3ቱም
    ከመሳፈሪያ ውጪ የያዙት ገንዘብ አልነበራቸውም ፡፡ አቤእና
    ከቤ በጣም ተቆጡ!
    ትንሽ አሰቡና አብቻ እቤት ሄዶ ጫቱን
    እንደያመጣው ጠየቁት አብቻ አልተስማማም
    "እኔ ስሄድ ምግቡን ልትጨርሱት ነው አልሄድም!!" ይላቸዋል
    አቤ እና ከቤ "በእውነት አንተ እስክትመጣ አንበላውም::" እያሉ
    ቢምሉለትም ሊያምናቸው አልቻለም በመጨረሻም ከስንት
    ልመናና ልምምጥ በኃላ አብቻ ጫቱን ለማምጣት ይስማማል::
    አቤ ሰሀቱን እየተመለከተ "አሁን 6 ሰሀት ነው እቤት ደርሰ
    እስክትመጣ 1 ሰሀት ይፈጅብሀል ስለዚህ 7 ሰሀት ላይ እዚ
    መድረስ አለብህ ሂድ በቃ፡፡"
    አብቻ ሄደ፡፡
    7 ሰሀት ሆኗል እስካሁን ግን አብቻ አልመጣም አቤ እና ከቤ
    ቢርባቸውም ለአብቻ የገቡለትን ቃል ላለማፍረስ ምንም ምግብ
    አልቀመሱም
    8 ሰሀት......t
    9 ሰሀት.....
    10 ሰሀት...
    11 ሰሀት...
    አብቻ የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ፡፡አቤእና ከቤ ረሀቡ ፀናባቸው፡፡
    ከምግቡ አንዳንድ ጉርሻ ብቻ ለመጉረስ ተስማምተው
    በእጃቸው ጠቅለሉና በአፋቸው ሲከቱት አብቻ ከጀርባ እየጮህ
    ወጣና
    "ሌቦች!!...ሃሃሃሃሃ አውቄው ነበር እኔ ስሄድ እንደምትበሉ እያየው ነበር
    እስካሁን ከጀርባቹ ነበርኩ::
    የትም አልሄድኩም !!"
    ብሎ እርፍ!!
    3 ጓደኛሞች አቤ,ከቤ እና አብቻ እሁድን ሀይቅ ዳር እየተዝናኑ ለማሳለፍ ይወስናሉ፡፡ 3ቱም የሚይዝቱን ነገር ይከፋፈላሉ አቤ, ምግብ ከቤ, የሚጠጣ ነገር "አብቻ" ደሞ ጫት ለመያዝ ይስማማሉ፡፡ ሀይቅ ዳር በ1 ሰዓት ጉዞ ይደርሱና መናፈሻ ገብተው ምንጣፍ አንጥፈው ቁጭ አሉ፡፡ ሁሉም ያመጡትን እያወጡ ማስቀመጥ እንደጀመሩ "አብቻ" ጫቱን ገዝቶ እቤት እንዳስቀመጠውና ረስቶት እንደመጣ ይነግራቸዋል፡፡ እዛ እንዳይገዙ ደሞ 3ቱም ከመሳፈሪያ ውጪ የያዙት ገንዘብ አልነበራቸውም ፡፡ አቤእና ከቤ በጣም ተቆጡ! ትንሽ አሰቡና አብቻ እቤት ሄዶ ጫቱን እንደያመጣው ጠየቁት አብቻ አልተስማማም "እኔ ስሄድ ምግቡን ልትጨርሱት ነው አልሄድም!!" ይላቸዋል አቤ እና ከቤ "በእውነት አንተ እስክትመጣ አንበላውም::" እያሉ ቢምሉለትም ሊያምናቸው አልቻለም በመጨረሻም ከስንት ልመናና ልምምጥ በኃላ አብቻ ጫቱን ለማምጣት ይስማማል:: አቤ ሰሀቱን እየተመለከተ "አሁን 6 ሰሀት ነው እቤት ደርሰ እስክትመጣ 1 ሰሀት ይፈጅብሀል ስለዚህ 7 ሰሀት ላይ እዚ መድረስ አለብህ ሂድ በቃ፡፡" አብቻ ሄደ፡፡ 7 ሰሀት ሆኗል እስካሁን ግን አብቻ አልመጣም አቤ እና ከቤ ቢርባቸውም ለአብቻ የገቡለትን ቃል ላለማፍረስ ምንም ምግብ አልቀመሱም 8 ሰሀት......t 9 ሰሀት..... 10 ሰሀት... 11 ሰሀት... አብቻ የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ፡፡አቤእና ከቤ ረሀቡ ፀናባቸው፡፡ ከምግቡ አንዳንድ ጉርሻ ብቻ ለመጉረስ ተስማምተው በእጃቸው ጠቅለሉና በአፋቸው ሲከቱት አብቻ ከጀርባ እየጮህ ወጣና "ሌቦች!!...ሃሃሃሃሃ አውቄው ነበር እኔ ስሄድ እንደምትበሉ እያየው ነበር እስካሁን ከጀርባቹ ነበርኩ:: የትም አልሄድኩም !!" ብሎ እርፍ!!
    0 Comments 0 Shares