Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
-
-
-
-
1 Comments 3 Shares3
-
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMአዲስ አገር በቀል የነዳጅ ኩባንያ ገበያውን ተቀላቀለጎመጁ ኦይል አትዮጵያ የተሰኘ አዲስ አገር በቀል የነዳጅ ኩባንያ ገበያውን እንደተቀላቀለ አስታወቀ፡፡ በነዳጅ፣ ዘይትና ቅባት ማከፋፈል ሥራ የተሰማራው ጎመጁ ኦይል ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በሁለት ኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች በ10.7 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሠረተ ሲሆን፣ ሥራውን የጀመረው 24 የነዳጅ ማደያዎችን በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች በመገንባት ነው፡፡የጎመጁ ኦይል ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ወ/ሪት ዓለምፀሐይ ሀብተ ማርያም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ባለሀብቶቹ በፈሳሽ ጭነት ማመላለሻ ዘርፍ ተሰማርተው ሲሠሩ የቆዩ ናቸው፡፡ በአገሪቱ የሚታየውን የነዳጅ ማደያዎች እጥረት ለመቅረፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ በማሰብ ኩባንያውን አቋቁመዋል ብለዋል፡፡0 Comments 0 Shares -
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COMበውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ ሎጂስቲክስ ኢንተርፕራይዝ ያሰበውን ያህል ገቢ ዕቃዎች ሳያስገባ ቀረኢንተርፕራይዙ በዘጠኝ ወራት ካቀደው በታች 11.8 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷልየአገሪቱን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ ዓለም አቀፍ ባህሮችን የሚያቆራርጠው ግዙፉ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ኢንተርፐራይዝ፣ በአገሪቱ በተፈጠረው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ባቀደው መጠን ገቢ ዕቃዎችን ማጓጓዝ ሳይችል ቀረ፡፡ሐሙስ ሚያዝያ 19 ቀን 2009 ዓ.ም. በትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለሚመራው የኢንተርፐራይዙ ሥራ አመራር ቦርድ በቀረበው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፣ አስመጪዎች በቂ የውጭ ምንዛሪ ባለማግኘታቸውና የዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ዘርፍ በመቀዛቀዙ የታሰበውን ያህል አልተሄደም፡፡በተለይ የንግዱ ማኅበረሰብ ኤልሲ (L/C) በበቂ0 Comments 0 Shares