• አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በትላልቅ ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች ቅንጡ ህይወታቸውን ለመግለፅ እና የብዙዎችን ቀልብ ለመሳብ በስፖርት መኪና ወይም በሊሞዚን ከቦታ ቦታ ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ፡፡

    ከዚህ በተቃራኒው ቻይናዊው የሶስት ዓመት ህጻን ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ሁልጊዜ የሚሄደው በበሬ፣ በፈረስ ወይም በአህያ ጀርባ ላይ ሆኖ ነው፡፡

    አባቱም በእግራቸው እየሄዱ ልጃቸው የሚጓዝበትን እንስሳ እየጎተቱና እየመሩ የሚያደርሱት ሲሆን፥ ይህ ዘወትራዊ የመጓጓዣ መንገድ የቻይና ማህበራዊ ሚዲያዎችን እያነጋገረ ነው፡፡

    በደቡባዊ ቻይና የሲቹዋን ግዛት ዋና ከተማ ቼንግዱ የሚኖሩት አባት እና ልጅ ከቤታቸው 3 ኪሎሜትር ወደሚርቀው ትምህርት ቤት የሚጓዙት በእንዲህ መልኩ ነው፡፡

    በሬ፣ አህያ እና ትንሽ ፈረስ በየእለቱ እየተቀያየሩ ህጻኑን ወደ ትምህርት ቤት ይወስዳሉ፡፡

    ሶስቱም እንስሳት የቻይና ስልጣኔ አድናቂ እና አስቀጣይ በሆኑት የህጻኑ አባት ሊ ሊ፥ እንክብካቤ ይደረግላቸዋል፡፡

    ሊ ሊ ጥንታዊው "የሀገራችን ስልጣኔ እና ባህል የዕለት ተዕለት ህይወታችን አንድ አካል መሆን አለበት" የሚል አቋም አላቸው፡፡

    "ልጄ በበሬው ወይም በአህያዋ ወደ ትምህርት ቤት ሲጓጓዝ ለህጻናት ያለው ፍቅር ይጨምርለታል” ነው ያሉት ሊ፡፡

    ህፃኑ በፈረስ፣ በሬ ወይም አህያ ጀርባ ላይ ሆኖ በየዕለቱ መጓዙ አባት ለልጃቸው ስለቻይና ስልጣኔ፣ ስለ ወቅታዊ ነገሮች እና የዛፍ ተከላ እንዲያስተምሩት እድልን ፈጥሯል፡፡

    ሆኖም እናት የልጃቸውን በእንስሳቱ ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ትምህርት ቤት መጓዝን ወድቆ ይጎዳብኛል በሚል አልወደዱትም፡፡

    ሊ ሊ ደግሞ ሁኔታውን በሌላ መንገድ ነው የሚገልጹት፤ “በሬ እና አህያ የተረጋጉ የመጓጓዣ እንስሳት በመሆናቸው በልጄ ላይ ምንም ዓይነት አደጋ አይደርስም” በማለት፡፡

    ህጻናት በአሁኑ ጊዜ ጥንታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶችን እየረሱ የማንነት ቀውስ ውስጥ እየገቡ በመሆኑ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህይወት እያሳወቁ ማሳደግ ይገባል ነው የሚሉት ሊ፡፡

    ቻይና በመንግስት ደረጃ ፈረስን፣ አህያን፣ በሬን ወይም ሌሎች እንስሳትን በመጓጓዣነት መጠቀምን ትፈቅዳለች።

    ሆኖም በእንስሳት የሚጓጓዙ ሰዎች ተሸከርካሪ በማይሄድባቸው መንገዶች ሊጠቀሙ እንደሚገባ ትመክራለች፡፡

    አንዳንድ ጊዜ በእንስሳት የሚጓዙ ሰዎች በተሸከርካሪ መንገድ ላይ በመግባት የትራፊክ ፍሰቱ ላይ ችግር እንደሚፈጥሩ እና የትራፊክ ፖሊሶችም በሌላ መንገድ እንዲጠቀሙ እንደሚያደርጓቸው ይነገራል፡፡

    በቻይና ማህበራዊ የትስስር ገጽ በሆነው ወይቦ፥ “የህጻኑን በበሬ ጀርባ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ እና በቻይና ስልጣኔ መካከል ግንኙነት አለን?” የሚል ጥያቄ ያነሱ አሉ።

    ሌሎቹ ደግሞ የህጻኑ አባት ልጁን ስለ ጥንታዊ የቻይና ስልጣኔ ለማስተማር የተጠቀሙበትን መንገድ አድንቀዋል።

    ምንጭ፡- http://en.people.cn/
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በትላልቅ ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች ቅንጡ ህይወታቸውን ለመግለፅ እና የብዙዎችን ቀልብ ለመሳብ በስፖርት መኪና ወይም በሊሞዚን ከቦታ ቦታ ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ቻይናዊው የሶስት ዓመት ህጻን ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ሁልጊዜ የሚሄደው በበሬ፣ በፈረስ ወይም በአህያ ጀርባ ላይ ሆኖ ነው፡፡ አባቱም በእግራቸው እየሄዱ ልጃቸው የሚጓዝበትን እንስሳ እየጎተቱና እየመሩ የሚያደርሱት ሲሆን፥ ይህ ዘወትራዊ የመጓጓዣ መንገድ የቻይና ማህበራዊ ሚዲያዎችን እያነጋገረ ነው፡፡ በደቡባዊ ቻይና የሲቹዋን ግዛት ዋና ከተማ ቼንግዱ የሚኖሩት አባት እና ልጅ ከቤታቸው 3 ኪሎሜትር ወደሚርቀው ትምህርት ቤት የሚጓዙት በእንዲህ መልኩ ነው፡፡ በሬ፣ አህያ እና ትንሽ ፈረስ በየእለቱ እየተቀያየሩ ህጻኑን ወደ ትምህርት ቤት ይወስዳሉ፡፡ ሶስቱም እንስሳት የቻይና ስልጣኔ አድናቂ እና አስቀጣይ በሆኑት የህጻኑ አባት ሊ ሊ፥ እንክብካቤ ይደረግላቸዋል፡፡ ሊ ሊ ጥንታዊው "የሀገራችን ስልጣኔ እና ባህል የዕለት ተዕለት ህይወታችን አንድ አካል መሆን አለበት" የሚል አቋም አላቸው፡፡ "ልጄ በበሬው ወይም በአህያዋ ወደ ትምህርት ቤት ሲጓጓዝ ለህጻናት ያለው ፍቅር ይጨምርለታል” ነው ያሉት ሊ፡፡ ህፃኑ በፈረስ፣ በሬ ወይም አህያ ጀርባ ላይ ሆኖ በየዕለቱ መጓዙ አባት ለልጃቸው ስለቻይና ስልጣኔ፣ ስለ ወቅታዊ ነገሮች እና የዛፍ ተከላ እንዲያስተምሩት እድልን ፈጥሯል፡፡ ሆኖም እናት የልጃቸውን በእንስሳቱ ጀርባ ላይ ሆኖ ወደ ትምህርት ቤት መጓዝን ወድቆ ይጎዳብኛል በሚል አልወደዱትም፡፡ ሊ ሊ ደግሞ ሁኔታውን በሌላ መንገድ ነው የሚገልጹት፤ “በሬ እና አህያ የተረጋጉ የመጓጓዣ እንስሳት በመሆናቸው በልጄ ላይ ምንም ዓይነት አደጋ አይደርስም” በማለት፡፡ ህጻናት በአሁኑ ጊዜ ጥንታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶችን እየረሱ የማንነት ቀውስ ውስጥ እየገቡ በመሆኑ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህይወት እያሳወቁ ማሳደግ ይገባል ነው የሚሉት ሊ፡፡ ቻይና በመንግስት ደረጃ ፈረስን፣ አህያን፣ በሬን ወይም ሌሎች እንስሳትን በመጓጓዣነት መጠቀምን ትፈቅዳለች። ሆኖም በእንስሳት የሚጓጓዙ ሰዎች ተሸከርካሪ በማይሄድባቸው መንገዶች ሊጠቀሙ እንደሚገባ ትመክራለች፡፡ አንዳንድ ጊዜ በእንስሳት የሚጓዙ ሰዎች በተሸከርካሪ መንገድ ላይ በመግባት የትራፊክ ፍሰቱ ላይ ችግር እንደሚፈጥሩ እና የትራፊክ ፖሊሶችም በሌላ መንገድ እንዲጠቀሙ እንደሚያደርጓቸው ይነገራል፡፡ በቻይና ማህበራዊ የትስስር ገጽ በሆነው ወይቦ፥ “የህጻኑን በበሬ ጀርባ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ እና በቻይና ስልጣኔ መካከል ግንኙነት አለን?” የሚል ጥያቄ ያነሱ አሉ። ሌሎቹ ደግሞ የህጻኑ አባት ልጁን ስለ ጥንታዊ የቻይና ስልጣኔ ለማስተማር የተጠቀሙበትን መንገድ አድንቀዋል። ምንጭ፡- http://en.people.cn/
    WWW.FANABC.COM
    FBC - አሜሪካዊው አዛውንት በስህተት ልጃቸው ያልሆነን ሰው ቀብረዋል
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 19 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የልጃቸውን እርም ያወጡት አሜሪካዊው አዛውንት ከልጃቸው ጋር በድጋሚ ተገናኝተዋል። በወሩ መጀመሪያ አካባቢ እርሳቸው በሚኖሩበትና ፋውንቴን ቫሊ በተባለው አካባቢ አንድ ሰው ሞቶ ይገኛል። የ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ65 አመቱ ኡጋንዳዊ ሙስታፋ ማጋምቦ ሙቶን ከ176 ልጆቹ መካከል የተወሰኑትን መንግስት እንዲደግፍላቸው ጠይቀዋል።

    “13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ30 ልጆቼን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወጪ መንግስት እንዲሸፍንልኝ ጠይቄያለሁ” ብለዋል በምዕራባዊ ኡጋንዳ ካጋዲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሙቶን።

    ከ40 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ በአካባቢያቸው የራሳቸውን ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዳቸውንም ነው ያስታወቁት።

    በማካሬሬ፣ ባራራ እና ኪያምቦጎ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማ 10 ልጆች አሉኝ፤ የአብዛኞቹ ወጪ በግሌ የሚሸፈኑ ናቸው ብለዋል።

    አምስት መንትያ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ ስድስት ሚስቶቻቸው ነፍሰጡር በመሆናቸው የልጆቻቸው ቁጥር በዚህ አመት መጨረሻ 180ን ይሻገራል ተብሏል።

    ሙቶን የኪያተረከራ መንደር ሊቀመንበር ሲሆኑ፥ እንደ አውሮፓውያኑ ጥር 1 1952 ተወልደው በ1968 የመጀመሪያ ትዳራቸውን ይዘዋል።

    በ16 አመታቸው ወደ ትዳር የገቡት ሙቶን አሁንም ተጨማሪ ሚስቶችን ለማግባት እና ልጆች ለመውለድ ብርታት አለኝ ይላሉ።

    አልኮል እና ስኳር አለመውሰዳቸው እንዲሁም ሲጋራ አለማጨሳቸው አሁንም ጠንካራ እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል።

    በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አዛውንት የተወሰኑ ሚስቶች በሙላጎ እና ባራራ ሆስፒታል እና በሩዋንዳ የተለያዩ የጤና ተቋማት በአዋላጅነት ይሰራሉ።

    “ወጣቷ ባለቤቴ እድሜዋ 25 ነው፤ ትልቋ ደግሞ 50 አመቷ ነው፤ በይፋ ጋብቻ ከመፈፀሜ በፊት ግን 10 ፍቅረኞች ነበሩኝ፤ ሁሉም በተመሳሳይ አመት የያዝኳቸው ፍቅረኞቼ በዚያው አመት ከእኔ ወልደዋል” ነው ያሉት የ65 አመቱ የልጆች ባለፀጋ።

    የመጀመሪያ ልጃቸው 49 አመት፤ የመጨረሻዎቹ ደግሞ የ4 አመት መንትያዎች መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።

    ሙቶን ከ90 በላይ የልጅ ልጅ እንዳላቸውም ጠቁመዋል።

    ሙቶን ስለ እያንዳንዱ ልጆቻቸው መረጃ የሚመዘግቡበት ደብተር እንዳላቸው እና ከኡጋንዳ ውጭ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲም የአብራካቸው ክፋዮች እንደሚገኙ አብራርተዋል።

    የተወሰኑት ሚስቶቻቸው ከመኖሪያ መንደራቸው ራቅ ብለው የሚገኙ መሆናቸው ፈተና እንደሆነባቸውም ይናገራሉ።

    “ከተለያዩ ሚስቶቼ በየቀኑ ከ10 በላይ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ ነገር ግን የሁሉንም ጥያቄ መመለስ አልችልም፤ በካጋዲ ብቻ ሰባት ሚስቶች አሉኝ” ነው ያሉት ሙቶን።

    “ሚስቶቼን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ ምንም ችግር የለብኝም፤ ምክንያቱም አብዛኞቹ እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፋሉ” ብለዋል ሙቶን።

    ከሙቶን ዘጠኝ ልጆችን የወለደችው የ45 አመት መዲና ቲባሲማ፥ አብዛኞቹ ልጆቿ በውትድርና፣ የመንግስት ስራ እና በህክምና ዘርፍ ስለተሰማሩ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት ተናግራለች።

    የ45 አመቱ የሙቶን ልጅ ሙሃመድ ያሩፉ በበኩሉ፥ የራሱን የንግድ ተቋም የሚያንቀሳቅስ ሲሆን፥ ለተወሰኑት ወንድም እና እህቶቹ የትምህርት ቤት ክፍያ ይከፍላል።

    የተወሰኑ ወንድሞቹ መምህራን በመሆናቸውም ከአባቱ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ለማቋቋም ማሰቡን ገልጿል።

    በካጋዲ ሆስፒታል የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት ሞሰስ ባሳሊርዋ፥ በርካታ ልጆችን ማፍራት ከጤና ችግሮች ባሻገር የልጆቹን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና ለማስተማር ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ በመሆኑ በርካታ እክሎችን እንደሚያመጣ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ www.newvision.co.ug/
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ65 አመቱ ኡጋንዳዊ ሙስታፋ ማጋምቦ ሙቶን ከ176 ልጆቹ መካከል የተወሰኑትን መንግስት እንዲደግፍላቸው ጠይቀዋል። “13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ30 ልጆቼን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወጪ መንግስት እንዲሸፍንልኝ ጠይቄያለሁ” ብለዋል በምዕራባዊ ኡጋንዳ ካጋዲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሙቶን። ከ40 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ በአካባቢያቸው የራሳቸውን ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዳቸውንም ነው ያስታወቁት። በማካሬሬ፣ ባራራ እና ኪያምቦጎ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማ 10 ልጆች አሉኝ፤ የአብዛኞቹ ወጪ በግሌ የሚሸፈኑ ናቸው ብለዋል። አምስት መንትያ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ ስድስት ሚስቶቻቸው ነፍሰጡር በመሆናቸው የልጆቻቸው ቁጥር በዚህ አመት መጨረሻ 180ን ይሻገራል ተብሏል። ሙቶን የኪያተረከራ መንደር ሊቀመንበር ሲሆኑ፥ እንደ አውሮፓውያኑ ጥር 1 1952 ተወልደው በ1968 የመጀመሪያ ትዳራቸውን ይዘዋል። በ16 አመታቸው ወደ ትዳር የገቡት ሙቶን አሁንም ተጨማሪ ሚስቶችን ለማግባት እና ልጆች ለመውለድ ብርታት አለኝ ይላሉ። አልኮል እና ስኳር አለመውሰዳቸው እንዲሁም ሲጋራ አለማጨሳቸው አሁንም ጠንካራ እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል። በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አዛውንት የተወሰኑ ሚስቶች በሙላጎ እና ባራራ ሆስፒታል እና በሩዋንዳ የተለያዩ የጤና ተቋማት በአዋላጅነት ይሰራሉ። “ወጣቷ ባለቤቴ እድሜዋ 25 ነው፤ ትልቋ ደግሞ 50 አመቷ ነው፤ በይፋ ጋብቻ ከመፈፀሜ በፊት ግን 10 ፍቅረኞች ነበሩኝ፤ ሁሉም በተመሳሳይ አመት የያዝኳቸው ፍቅረኞቼ በዚያው አመት ከእኔ ወልደዋል” ነው ያሉት የ65 አመቱ የልጆች ባለፀጋ። የመጀመሪያ ልጃቸው 49 አመት፤ የመጨረሻዎቹ ደግሞ የ4 አመት መንትያዎች መሆናቸውንም ነው የተናገሩት። ሙቶን ከ90 በላይ የልጅ ልጅ እንዳላቸውም ጠቁመዋል። ሙቶን ስለ እያንዳንዱ ልጆቻቸው መረጃ የሚመዘግቡበት ደብተር እንዳላቸው እና ከኡጋንዳ ውጭ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲም የአብራካቸው ክፋዮች እንደሚገኙ አብራርተዋል። የተወሰኑት ሚስቶቻቸው ከመኖሪያ መንደራቸው ራቅ ብለው የሚገኙ መሆናቸው ፈተና እንደሆነባቸውም ይናገራሉ። “ከተለያዩ ሚስቶቼ በየቀኑ ከ10 በላይ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ ነገር ግን የሁሉንም ጥያቄ መመለስ አልችልም፤ በካጋዲ ብቻ ሰባት ሚስቶች አሉኝ” ነው ያሉት ሙቶን። “ሚስቶቼን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ ምንም ችግር የለብኝም፤ ምክንያቱም አብዛኞቹ እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፋሉ” ብለዋል ሙቶን። ከሙቶን ዘጠኝ ልጆችን የወለደችው የ45 አመት መዲና ቲባሲማ፥ አብዛኞቹ ልጆቿ በውትድርና፣ የመንግስት ስራ እና በህክምና ዘርፍ ስለተሰማሩ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት ተናግራለች። የ45 አመቱ የሙቶን ልጅ ሙሃመድ ያሩፉ በበኩሉ፥ የራሱን የንግድ ተቋም የሚያንቀሳቅስ ሲሆን፥ ለተወሰኑት ወንድም እና እህቶቹ የትምህርት ቤት ክፍያ ይከፍላል። የተወሰኑ ወንድሞቹ መምህራን በመሆናቸውም ከአባቱ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ለማቋቋም ማሰቡን ገልጿል። በካጋዲ ሆስፒታል የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት ሞሰስ ባሳሊርዋ፥ በርካታ ልጆችን ማፍራት ከጤና ችግሮች ባሻገር የልጆቹን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና ለማስተማር ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ በመሆኑ በርካታ እክሎችን እንደሚያመጣ ተናግረዋል። ምንጭ፦ www.newvision.co.ug/
    WWW.FANABC.COM
    FBC - የ176 ልጆች አባት የሆኑት ኡጋንዳዊ መንግስት ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠየቁ
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ65 አመቱ ኡጋንዳዊ ሙስታፋ ማጋምቦ ሙቶን ከ176 ልጆቹ መካከል የተወሰኑትን መንግስት እንዲደግፍላቸው ጠይቀዋል። “13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - በቀጥታ የኢንተርኔት ስርጭት ሬት የተመገበችው ቻይናዊ ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢንተርኔት በቀጥታ ሬት መሳይ ተክል ስትመገብ የነበረችው ቻይናዊ ራሷን በመሳቷ ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች። የ26 አመት ወጣቷ ዣንግ ተመግባው የማታውቀውንና ጎጂ ይዘት ይኖረዋል ብላ የማታስበ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - አዛውንቷ ወደ አውሮፕላን ሞተር የወረወሩት ሳንቲም በረራውን ለሰዓታት አዘገየ
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2009 ኤፍ.ቢ.ሲ) ቻይናዊቷ አዛውንት ወደሚጓዙበት አውሮፕላን የወረወሩት ሳንቲም በረራው ለሰዓታት እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል፡፡ የቻይና ሳውዘርን አየር መንገድ የበረራ ቁጥር 380 በሻንጋይ ፑዶንግ ዓለም አቀፍ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - ፊሊፒንስ የሀገሪቱን ብሔራዊ መዝሙር ከልባቸው የማይዘምሩ ሰዎችን የሚቀጣ አዋጅ አዘጋጀች
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፊሊፒንስን ብሔራዊ መዝሙር ከልባቸው የማይዘምሩ የሀገሬው ዜጎች እስከ እስር የሚደርስ ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተብሏል፡፡ ዜጎችም ከዚህ ቅጣት ለማምለጥ የድምፅ ልምምድ ለማድረግ ወደ ማሰልጠኛ ስፍ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - ቻይና 40 ሺህ ዛፎችን የሚያበቅሉ ህንጻዎችን የያዘች ከተማ እየገነባች ነው
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፓሪሱን ስምምነት ውድቅ ካደረጉ በኋላ ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የየራሳቸውን ስራ እየሰሩ ነው፡፡ ቻይናም በቅርቡ በባህር ላይ የሚንሳፈፍ ግዙፍ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - በጣም ውድ የእጅ አምባር ስትለካ ወድቆ የተሰበረባት ቻይናዊ በድንጋጤ ራሷን ስታለች
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቻይና ዩናን ግዛት በሚገኝ የጌጣ ጌጥ ገበያ ከውድ አረንጓዴ ድንጋይ የሚሰራ የእጅ አምባር ለመግዛት ስትመለከት በድንገት ከእጇ ያመለጣት ወጣት በድንጋጤ ወዲያውኑ ራሷን ስታለች። የእጅ አምባ...
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.FANABC.COM
    FBC - ዘወትር በእግሩ ረጅም ርቀት የሚጓዘው አሜሪካዊ በለጋሾች መኪና ተገዛለት
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት በሮክዋል ከተማ በጎ ፈቃደኛ ለጋሾች ዘወትር በርካታ ኪሎ ሜትሮችን በእግሩ የሚጓዘውን ግለሰብ በስጦታ አስደምመውታል። በየቀኑ 10 ኪሎ ሜትሮችን ከቤቱ ወደ ስራ ቦታ በ...
    0 Comments 0 Shares