• ነገሩ እንዲህ ነው አንድ የታወቀ ወንጀለኛ በስንት መከራ ተያዘ። ተይዞ ፖሊስ መረመረው። በተያዘ በሳምንቱ በጠና ታሞ ሆስፒታል ይሄዳል። ታዲያ ዶክተሩ "ትርፍ አንጀት ስለሆነ ትርፍ አንጀቱ ተቆርጦ መውጣት አለበት" ብሎ ኦፕራሲዮን ተደርጎ ወጣለት።

    እንደገና በሳምንቱ ታመመ ዶክተሩ "ጉበቱ ግማሹ ስለተጎዳ ተቆርጦ መውጣት አለበት" ብሎ ኦፕራሲዮን ተደርጎ ወጣለት።
    እንደገና አሁንም በሳምንቱ ታመመና ሆስፒታል ሄደ።
    ዶክተሩ "አንዱ ኩላሊት ስራውን ስላቆመ መውጣት አለበት" ሲል ወንጀለኛውን ሲያመላልስ የነበረው ፖሊስ ወደ ዶክተሩ ጠጋ ብሎ እኔ ምልህ ዶክተር "ይህ ሰው ዘመድህ ነው እንዴ"? ይለዋል።
    ዶክተሩም "ኧረ ዘመዴ አይደለም። ምነው?" ሲለው ፖሊሱ ምን ቢል ጥሩ ነው?

    "ቀስ በቀስ ከእስር ቤት እያወጣሀው እኮነው። እንደመኪና መለዋወጫ አካሉን ቀስ በቀስ እየከፋፈልክ ከእስር ቤት አስወጥተህ መልሰህ ልትገጣጥመው ይሆናላ"
    ነገሩ እንዲህ ነው አንድ የታወቀ ወንጀለኛ በስንት መከራ ተያዘ። ተይዞ ፖሊስ መረመረው። በተያዘ በሳምንቱ በጠና ታሞ ሆስፒታል ይሄዳል። ታዲያ ዶክተሩ "ትርፍ አንጀት ስለሆነ ትርፍ አንጀቱ ተቆርጦ መውጣት አለበት" ብሎ ኦፕራሲዮን ተደርጎ ወጣለት። እንደገና በሳምንቱ ታመመ ዶክተሩ "ጉበቱ ግማሹ ስለተጎዳ ተቆርጦ መውጣት አለበት" ብሎ ኦፕራሲዮን ተደርጎ ወጣለት። እንደገና አሁንም በሳምንቱ ታመመና ሆስፒታል ሄደ። ዶክተሩ "አንዱ ኩላሊት ስራውን ስላቆመ መውጣት አለበት" ሲል ወንጀለኛውን ሲያመላልስ የነበረው ፖሊስ ወደ ዶክተሩ ጠጋ ብሎ እኔ ምልህ ዶክተር "ይህ ሰው ዘመድህ ነው እንዴ"? ይለዋል። ዶክተሩም "ኧረ ዘመዴ አይደለም። ምነው?" ሲለው ፖሊሱ ምን ቢል ጥሩ ነው? "ቀስ በቀስ ከእስር ቤት እያወጣሀው እኮነው። እንደመኪና መለዋወጫ አካሉን ቀስ በቀስ እየከፋፈልክ ከእስር ቤት አስወጥተህ መልሰህ ልትገጣጥመው ይሆናላ"
    0 Comments 0 Shares
  • ሰውየው በመጠጥ ቤቱ የፊት ለፊት በር በኩል ገብቶ ተቀመጠና መጠጥ አዘዘ።
    መጠጥ ቀጂው ግን ሰውየው በጣም መስከሩን ስላዬ በትህትና ብዙ መጠጣቱንና ወደቤት ቢገባ እንደሚሻል ይነግረዋል።
    ሰውዬው በስካር መንፈስ ቢሆንም በመጠጥ ቀጂው ንግግር ተገርሞ እሺ ብሎ እየተንገዳገደ በመጣበት በር ይወጣል።

    ከትንሽ ቆይታ በኋላ በሌላ የጎን በር ድጋሚ እየተንገዳገደ ገባና መጠጥ አዘዘ።
    መጠጥ ቀጂው አሁንም በትህትና ሌላ መጠጥ መጠጣት እንደማይችልና ከፈለገ ወደ ቤቱ ሊያደርሰው የሚችል መኪና ደውሎ ሊጠራለት እንደሚችል ይገልፅለታል።
    ሰካራሙ ሰውዬ አሁን በንዴት መጠጥ ቀጂውን ካየው በኋላ እየተንገዳገደና እያጉተመተመ በመጣበት በር ይወጣል።

    ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ በጓሮ በር በኩል ለሶስተኛ ጊዜ ወደ መጠጥ ቤቱ ይገባና መጠጥ ያዛል።
    በዚህ ጊዜ መጠጥ ቀጂው በጣም ይናደዳል።
    መጠጥ ቀጂው: "አንተ ሰውዬ ሰው የሚነግርህን አትሰማም እንዴ? ከመጠን በላይ ስለሰከርክ ተጨማሪ መጠጥ ልንሸጥልህ አንችልም አልኩህ እኮ።
    አሁን ፖሊስ ጠርቼ ሳላስቀፈድድህ ከዚህ ቤት ውጣ። አላበዛኸውም እንዴ አሁንስ!!!" ሲለው
    ሰካራሙ: መጠጥ ቀጂውን ቀና ብሎ ከተመለከተው በኋላ በብስጭት እያለቀሰ "አንተ ራስህ አላበዛኸውም እንዴ አሁንስ?
    ቆይ ግን ስንት መጠጥ ቤት ነው የምትሰራው?" ብሎት እርፍ!!!

    src:n/a
    ሰውየው በመጠጥ ቤቱ የፊት ለፊት በር በኩል ገብቶ ተቀመጠና መጠጥ አዘዘ። መጠጥ ቀጂው ግን ሰውየው በጣም መስከሩን ስላዬ በትህትና ብዙ መጠጣቱንና ወደቤት ቢገባ እንደሚሻል ይነግረዋል። ሰውዬው በስካር መንፈስ ቢሆንም በመጠጥ ቀጂው ንግግር ተገርሞ እሺ ብሎ እየተንገዳገደ በመጣበት በር ይወጣል። ከትንሽ ቆይታ በኋላ በሌላ የጎን በር ድጋሚ እየተንገዳገደ ገባና መጠጥ አዘዘ። መጠጥ ቀጂው አሁንም በትህትና ሌላ መጠጥ መጠጣት እንደማይችልና ከፈለገ ወደ ቤቱ ሊያደርሰው የሚችል መኪና ደውሎ ሊጠራለት እንደሚችል ይገልፅለታል። ሰካራሙ ሰውዬ አሁን በንዴት መጠጥ ቀጂውን ካየው በኋላ እየተንገዳገደና እያጉተመተመ በመጣበት በር ይወጣል። ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ በጓሮ በር በኩል ለሶስተኛ ጊዜ ወደ መጠጥ ቤቱ ይገባና መጠጥ ያዛል። በዚህ ጊዜ መጠጥ ቀጂው በጣም ይናደዳል። መጠጥ ቀጂው: "አንተ ሰውዬ ሰው የሚነግርህን አትሰማም እንዴ? ከመጠን በላይ ስለሰከርክ ተጨማሪ መጠጥ ልንሸጥልህ አንችልም አልኩህ እኮ። አሁን ፖሊስ ጠርቼ ሳላስቀፈድድህ ከዚህ ቤት ውጣ። አላበዛኸውም እንዴ አሁንስ!!!" ሲለው ሰካራሙ: መጠጥ ቀጂውን ቀና ብሎ ከተመለከተው በኋላ በብስጭት እያለቀሰ "አንተ ራስህ አላበዛኸውም እንዴ አሁንስ? ቆይ ግን ስንት መጠጥ ቤት ነው የምትሰራው?" ብሎት እርፍ!!! src:n/a
    0 Comments 0 Shares
  • በአውሮፓ የሳይበር ጥቃቶችን ለመከላከል ጠበቅ ያለ ህግ ወጥቷል
    አንገብጋቢ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን የሚቆጣጠሩ የቴክሎጂ ድርጅቶች ማንኛውንም የሳይበር ጥሰት ለሚመለከተው ክፍል ሪፖርት እንዲያደርጉ አዲሱ ህግ ያስገድዳል፡፡ ህጉ ለባንኮች፤ ለሃይልና ውሃ ልማት አገልግሎቶች የሳይበር ደህንነታቸው የሚረጋገጥበትን ሚኒመም ስታንዳርድም አስቀምጧል፡፡

    ይህ በአውሮፓ ምድር በሳይበር ደህንነት ዙሪያ የወጣ ህግ ሆኖም ተመዝግቧል፡፡ የህጉ መውጣት በተለያዩ መሰረተ ልማቶች እንደ አየር ማረፊያና የሃይል ስቴሽኖች ላይ ከሚደርስ የሰርጎ ገብ ጥቃት ለመታደግ ነው ተብሏል፡፡ ህጉ የኦንላይን የገበያ መገበያያ የሆኑትን እንደ ኢ ቤይ አማዞንና የሰርች ኢንጅን የሆነውን ጎግልን ጨምሮ የሚመለከት ዝርዝር ነገር ያካትታል ተብሏል፡፡

    በኔትወርክና ኢንፎርሜሽን ደህንነት ዙሪያ ይህን መመሪያ ለማውጣት የተገደድነው የሳይበር ጥቃት ስጋት እየጨመረ በመሄዱ ነው ሲሉም ህግ አውጪዎቹ ተናግረዋል፡፡

    የአውሮፓ የኔትወርክና ኢንፎርሜሽን ደህንነት ኤጀንሲ ባወጣው መረጃ መሰረትም የሳይበር ጥቃት በአመት ከ260 እስከ 360 ቢሊዮን ዩሮ ክስረት እንደሚያደርስ ነው፡፡ በአዲሱ ህግ መሰረት አባል ሃገራት የመረጃ ጥሰቶችን በመለዋወጥና በማልማት ዙሪያ ተባብረውና ተሳስረው በመስራት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ህጉ ጠቁሟል ሲል ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
    በአውሮፓ የሳይበር ጥቃቶችን ለመከላከል ጠበቅ ያለ ህግ ወጥቷል አንገብጋቢ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን የሚቆጣጠሩ የቴክሎጂ ድርጅቶች ማንኛውንም የሳይበር ጥሰት ለሚመለከተው ክፍል ሪፖርት እንዲያደርጉ አዲሱ ህግ ያስገድዳል፡፡ ህጉ ለባንኮች፤ ለሃይልና ውሃ ልማት አገልግሎቶች የሳይበር ደህንነታቸው የሚረጋገጥበትን ሚኒመም ስታንዳርድም አስቀምጧል፡፡ ይህ በአውሮፓ ምድር በሳይበር ደህንነት ዙሪያ የወጣ ህግ ሆኖም ተመዝግቧል፡፡ የህጉ መውጣት በተለያዩ መሰረተ ልማቶች እንደ አየር ማረፊያና የሃይል ስቴሽኖች ላይ ከሚደርስ የሰርጎ ገብ ጥቃት ለመታደግ ነው ተብሏል፡፡ ህጉ የኦንላይን የገበያ መገበያያ የሆኑትን እንደ ኢ ቤይ አማዞንና የሰርች ኢንጅን የሆነውን ጎግልን ጨምሮ የሚመለከት ዝርዝር ነገር ያካትታል ተብሏል፡፡ በኔትወርክና ኢንፎርሜሽን ደህንነት ዙሪያ ይህን መመሪያ ለማውጣት የተገደድነው የሳይበር ጥቃት ስጋት እየጨመረ በመሄዱ ነው ሲሉም ህግ አውጪዎቹ ተናግረዋል፡፡ የአውሮፓ የኔትወርክና ኢንፎርሜሽን ደህንነት ኤጀንሲ ባወጣው መረጃ መሰረትም የሳይበር ጥቃት በአመት ከ260 እስከ 360 ቢሊዮን ዩሮ ክስረት እንደሚያደርስ ነው፡፡ በአዲሱ ህግ መሰረት አባል ሃገራት የመረጃ ጥሰቶችን በመለዋወጥና በማልማት ዙሪያ ተባብረውና ተሳስረው በመስራት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ህጉ ጠቁሟል ሲል ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በልጽገው ለትግበራ የተዘጋጁ ከፍተኛ ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸውንና ጨዋታ ቀያሪ ቴክኖሎጂካዊ ፕላትፎርሞችን እናስተዋውቃችሁ
    1. ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም
    የዓለም አቀፍ ሳይበር ኢንዱስትሪ ሶፍትዌርን መሰረት ባደረገበት ሁኔታ የሶፍትዌሮች ቁልፍ መሰረትና ሞተር የሆነው ኦፕሬቲንግ ሲስተም ባለቤት መረጋገጥ ለሃገራዊ ደህንነትና ለኢኮኖሚ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፤ ከፍተኛ ኩራትም ነው፡፡ አሁን የተሰራው ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ዳታ ማስተላለፊያ አውታሮችና በኔትወርክ ሴኩሪቲ ሲስተሞች ማለትም ራውተሮች፣ ስዊች፣ ፋየርወልና የአይፒኤስ ጥገኝነት በማስወገድ ሃገራችንን የእነዚህ ቴክኖሎጂዎች ባለቤት ከማድረግ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደነ ሁዋዌ፣ ዜድ.ቲ.ኢ፣ ሲስኮ፣ ጆኒፐር ተወዳዳሪ እንድንሆን መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ሀገራዊ ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ወጪያችንን በመቀነስ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማግኘት ቁልፍ ሚና መጫወት ይችላል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ለኔትወርክ ሲስተም አልሚዎችና ተመራማሪዎች እንደ ፕላትፎርም ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ የኢንዱስትሪው ተዋናዮች በቀላሉ እሴት እንዲጨምሩ በማስቻል ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ የተፈጠረውን የኦፕሬቲንግ ሲስተም አቅም ሌሎች ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ለማበልጸግ መጠቀም እንችላለን፡፡ የዚህ ቴክኖሎጂ ባለቤትነት መረጋገጥ በአጠቃላይ በሳይበር ኢንዱስትሪ የህዳሴ ነጥብ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ ስለሆነም ስያሜውን ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ብለነዋል፡፡
    2. ኔትወርክ ሲስተሞች
    በአሁኑ ወቅት ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እንደ ፕላትፎርም በመጠቀም ፋየርወል፣ ስዊችና ጂ.ፒ.አይ የተባሉ ሲስተሞች በልጽገው በተግባር ሙከራ ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሲስተሞች የቴሌኮሙኒኬሽን ተቋማት፣ የመንግስት ተቋማትና የግል ተቋማት ለዳታ መተላለፊያነትና ለደህንነት የሚጠቀሙባቸው ሲሆኑ በሳይበር ምህዳር ቁልፍ የስህበት ማዕከል ቴክኖሎጂዎች ናቸው፡፡ አሁን ከተለያዩ ተቋማት ማለትም ሲስኮ፣ ሁዋዌ እና ሌሎች የምንገዛቸው ኔትወርክ ሲስተሞች ጥገኝነት በማስወገድ ራሳችንን የሚያስችሉ ናቸው፡፡ ይህም ሃገራዊ ደህንነትን ከማሳደግ አንጻር እና የኢኮኖሚ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ትርጉም ያለው ነው፡፡
    3. ሴኩሪቲ ኢንተለጀንስ ሲስተም
    ሃገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከተለያዩ ሲስሞች የሚመጡ መረጃዎች የመተንተን አቅም ወሳኝ በመሆኑና ይህ አቅም በጣም ክሪቲካልና ሚስጥራዊ አቅም ያለው በመሆኑ በሀገር አቅም መሰራት ያለበት ነው፡፡ ይህ ታሳቢ ተደርጎ የሴኩሪቲ መረጃዎችን በመተንተን የማስጠንቀቅና የመግታት ስራ የሚያከናውን ሲስተም በልጽጎ በትግበራ ሙከራ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሃገራዊ ሳይበር ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድገው ሲሆን እንደ ፕላትፎርም ጥቅም ላይ የሚውል ስለሆነም እዛው እያለ ለኢኮኖሚ ልማት ስራዎቻችን መጠቀም እንችላለን፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በልጽገው ለትግበራ የተዘጋጁ ከፍተኛ ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸውንና ጨዋታ ቀያሪ ቴክኖሎጂካዊ ፕላትፎርሞችን እናስተዋውቃችሁ
    1. ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም
    የዓለም አቀፍ ሳይበር ኢንዱስትሪ ሶፍትዌርን መሰረት ባደረገበት ሁኔታ የሶፍትዌሮች ቁልፍ መሰረትና ሞተር የሆነው ኦፕሬቲንግ ሲስተም ባለቤት መረጋገጥ ለሃገራዊ ደህንነትና ለኢኮኖሚ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፤ ከፍተኛ ኩራትም ነው፡፡ አሁን የተሰራው ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ዳታ ማስተላለፊያ አውታሮችና በኔትወርክ ሴኩሪቲ ሲስተሞች ማለትም ራውተሮች፣ ስዊች፣ ፋየርወልና የአይፒኤስ ጥገኝነት በማስወገድ ሃገራችንን የእነዚህ ቴክኖሎጂዎች ባለቤት ከማድረግ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደነ ሁዋዌ፣ ዜድ.ቲ.ኢ፣ ሲስኮ፣ ጆኒፐር ተወዳዳሪ እንድንሆን መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ሀገራዊ ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ወጪያችንን በመቀነስ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማግኘት ቁልፍ ሚና መጫወት ይችላል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ለኔትወርክ ሲስተም አልሚዎችና ተመራማሪዎች እንደ ፕላትፎርም ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ የኢንዱስትሪው ተዋናዮች በቀላሉ እሴት እንዲጨምሩ በማስቻል ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ የተፈጠረውን የኦፕሬቲንግ ሲስተም አቅም ሌሎች ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ለማበልጸግ መጠቀም እንችላለን፡፡ የዚህ ቴክኖሎጂ ባለቤትነት መረጋገጥ በአጠቃላይ በሳይበር ኢንዱስትሪ የህዳሴ ነጥብ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ ስለሆነም ስያሜውን ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ብለነዋል፡፡
    2. ኔትወርክ ሲስተሞች
    በአሁኑ ወቅት ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እንደ ፕላትፎርም በመጠቀም ፋየርወል፣ ስዊችና ጂ.ፒ.አይ የተባሉ ሲስተሞች በልጽገው በተግባር ሙከራ ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሲስተሞች የቴሌኮሙኒኬሽን ተቋማት፣ የመንግስት ተቋማትና የግል ተቋማት ለዳታ መተላለፊያነትና ለደህንነት የሚጠቀሙባቸው ሲሆኑ በሳይበር ምህዳር ቁልፍ የስህበት ማዕከል ቴክኖሎጂዎች ናቸው፡፡ አሁን ከተለያዩ ተቋማት ማለትም ሲስኮ፣ ሁዋዌ እና ሌሎች የምንገዛቸው ኔትወርክ ሲስተሞች ጥገኝነት በማስወገድ ራሳችንን የሚያስችሉ ናቸው፡፡ ይህም ሃገራዊ ደህንነትን ከማሳደግ አንጻር እና የኢኮኖሚ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ትርጉም ያለው ነው፡፡
    3. ሴኩሪቲ ኢንተለጀንስ ሲስተም
    ሃገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከተለያዩ ሲስሞች የሚመጡ መረጃዎች የመተንተን አቅም ወሳኝ በመሆኑና ይህ አቅም በጣም ክሪቲካልና ሚስጥራዊ አቅም ያለው በመሆኑ በሀገር አቅም መሰራት ያለበት ነው፡፡ ይህ ታሳቢ ተደርጎ የሴኩሪቲ መረጃዎችን በመተንተን የማስጠንቀቅና የመግታት ስራ የሚያከናውን ሲስተም በልጽጎ በትግበራ ሙከራ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሃገራዊ ሳይበር ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድገው ሲሆን እንደ ፕላትፎርም ጥቅም ላይ የሚውል ስለሆነም እዛው እያለ ለኢኮኖሚ ልማት ስራዎቻችን መጠቀም እንችላለን፡፡
    በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በልጽገው ለትግበራ የተዘጋጁ ከፍተኛ ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸውንና ጨዋታ ቀያሪ ቴክኖሎጂካዊ ፕላትፎርሞችን እናስተዋውቃችሁ 1. ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም የዓለም አቀፍ ሳይበር ኢንዱስትሪ ሶፍትዌርን መሰረት ባደረገበት ሁኔታ የሶፍትዌሮች ቁልፍ መሰረትና ሞተር የሆነው ኦፕሬቲንግ ሲስተም ባለቤት መረጋገጥ ለሃገራዊ ደህንነትና ለኢኮኖሚ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፤ ከፍተኛ ኩራትም ነው፡፡ አሁን የተሰራው ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ዳታ ማስተላለፊያ አውታሮችና በኔትወርክ ሴኩሪቲ ሲስተሞች ማለትም ራውተሮች፣ ስዊች፣ ፋየርወልና የአይፒኤስ ጥገኝነት በማስወገድ ሃገራችንን የእነዚህ ቴክኖሎጂዎች ባለቤት ከማድረግ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደነ ሁዋዌ፣ ዜድ.ቲ.ኢ፣ ሲስኮ፣ ጆኒፐር ተወዳዳሪ እንድንሆን መሰረት የሚጥል ነው፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ሀገራዊ ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ወጪያችንን በመቀነስ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማግኘት ቁልፍ ሚና መጫወት ይችላል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ለኔትወርክ ሲስተም አልሚዎችና ተመራማሪዎች እንደ ፕላትፎርም ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ የኢንዱስትሪው ተዋናዮች በቀላሉ እሴት እንዲጨምሩ በማስቻል ኢንዱስትሪውን ለማነቃቃት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ የተፈጠረውን የኦፕሬቲንግ ሲስተም አቅም ሌሎች ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ለማበልጸግ መጠቀም እንችላለን፡፡ የዚህ ቴክኖሎጂ ባለቤትነት መረጋገጥ በአጠቃላይ በሳይበር ኢንዱስትሪ የህዳሴ ነጥብ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ ስለሆነም ስያሜውን ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ብለነዋል፡፡ 2. ኔትወርክ ሲስተሞች በአሁኑ ወቅት ህዳሴ ኔትወርክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እንደ ፕላትፎርም በመጠቀም ፋየርወል፣ ስዊችና ጂ.ፒ.አይ የተባሉ ሲስተሞች በልጽገው በተግባር ሙከራ ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሲስተሞች የቴሌኮሙኒኬሽን ተቋማት፣ የመንግስት ተቋማትና የግል ተቋማት ለዳታ መተላለፊያነትና ለደህንነት የሚጠቀሙባቸው ሲሆኑ በሳይበር ምህዳር ቁልፍ የስህበት ማዕከል ቴክኖሎጂዎች ናቸው፡፡ አሁን ከተለያዩ ተቋማት ማለትም ሲስኮ፣ ሁዋዌ እና ሌሎች የምንገዛቸው ኔትወርክ ሲስተሞች ጥገኝነት በማስወገድ ራሳችንን የሚያስችሉ ናቸው፡፡ ይህም ሃገራዊ ደህንነትን ከማሳደግ አንጻር እና የኢኮኖሚ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ትርጉም ያለው ነው፡፡ 3. ሴኩሪቲ ኢንተለጀንስ ሲስተም ሃገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከተለያዩ ሲስሞች የሚመጡ መረጃዎች የመተንተን አቅም ወሳኝ በመሆኑና ይህ አቅም በጣም ክሪቲካልና ሚስጥራዊ አቅም ያለው በመሆኑ በሀገር አቅም መሰራት ያለበት ነው፡፡ ይህ ታሳቢ ተደርጎ የሴኩሪቲ መረጃዎችን በመተንተን የማስጠንቀቅና የመግታት ስራ የሚያከናውን ሲስተም በልጽጎ በትግበራ ሙከራ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ሃገራዊ ሳይበር ደህንነት አቅሞችን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድገው ሲሆን እንደ ፕላትፎርም ጥቅም ላይ የሚውል ስለሆነም እዛው እያለ ለኢኮኖሚ ልማት ስራዎቻችን መጠቀም እንችላለን፡፡
    0 Comments 1 Shares
  • ግዙፉ የቴክኖሎጂ ተቋም አፕል የአይፎን (iPhones)፣ አይፓድ (iPads) እና ማክ (Mac) ኮምፒውተሮቹ በሜልትዳውን እና ስፔክተር የችፕ ክፍተቶች ሰለባ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኮምፒውተር ማዕከላዊ ፕሮሰሲንግ ዩኒት (CPU) ላይ የተገኙትን የደህንነት ክፍተቶ ለመሙላት ተቋማት በከፍተኛ ሩጫ ላይ ናቸው፡፡

    የክፍተቱ (bugs) ሰለባ የሆኑ በአለም አቀፍ ደረጃ ያሉ እና የኢንቴል (Intel) እና ኤ.አር.ኤም (ARM) ቺፕ ተጠቃሚ የሆኑ ዘመናዊ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች መጠቀሚያ ቴክኖሎጂዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ተጠቅሷል፡፡

    አፕልም ለተጠቃሚዎቹ የክፍተት (flaws) መሙያ የለቀቀ ሲሆን ተጠቃሚዎቹ ከታማኝ ምንጮች ብቻ በማውረድ መጠቀም ይገባቸዋል ብሏል፡፡ ተቋሙ መከላከያ ካቀረበላቸው መካከልም ለአይፎን እና አይፓድ ስርዓተ ክወና (operating systems)፣ ለiOS 11.2፣ የMacOS 10.12.2 ለሆኑት ለማክቡክ (MacBooks) እና ለአይማክ (iMacs) ምርቶች ነው፡፡

    በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑና የኢንቴል (Intel) እና ኤ.አር.ኤም (ARM) ቺፖችን ለምርቶቻቸው የሚጠቀሙ ኩባንያዎች የጥቃት ተጋላጭነቱን ለመከላከል በከፍተኛ ደረጃ በስራ ተጠምደዋል፡፡
    ግዙፉ የቴክኖሎጂ ተቋም አፕል የአይፎን (iPhones)፣ አይፓድ (iPads) እና ማክ (Mac) ኮምፒውተሮቹ በሜልትዳውን እና ስፔክተር የችፕ ክፍተቶች ሰለባ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኮምፒውተር ማዕከላዊ ፕሮሰሲንግ ዩኒት (CPU) ላይ የተገኙትን የደህንነት ክፍተቶ ለመሙላት ተቋማት በከፍተኛ ሩጫ ላይ ናቸው፡፡ የክፍተቱ (bugs) ሰለባ የሆኑ በአለም አቀፍ ደረጃ ያሉ እና የኢንቴል (Intel) እና ኤ.አር.ኤም (ARM) ቺፕ ተጠቃሚ የሆኑ ዘመናዊ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች መጠቀሚያ ቴክኖሎጂዎች ተጋላጭ መሆናቸውን ተጠቅሷል፡፡ አፕልም ለተጠቃሚዎቹ የክፍተት (flaws) መሙያ የለቀቀ ሲሆን ተጠቃሚዎቹ ከታማኝ ምንጮች ብቻ በማውረድ መጠቀም ይገባቸዋል ብሏል፡፡ ተቋሙ መከላከያ ካቀረበላቸው መካከልም ለአይፎን እና አይፓድ ስርዓተ ክወና (operating systems)፣ ለiOS 11.2፣ የMacOS 10.12.2 ለሆኑት ለማክቡክ (MacBooks) እና ለአይማክ (iMacs) ምርቶች ነው፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑና የኢንቴል (Intel) እና ኤ.አር.ኤም (ARM) ቺፖችን ለምርቶቻቸው የሚጠቀሙ ኩባንያዎች የጥቃት ተጋላጭነቱን ለመከላከል በከፍተኛ ደረጃ በስራ ተጠምደዋል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • https://www.youtube.com/watch?v=-XLQb_tKOfQ
    https://www.youtube.com/watch?v=-XLQb_tKOfQ
    0 Comments 0 Shares
  • https://www.youtube.com/watch?v=-YTUKy0tDWg
    https://www.youtube.com/watch?v=-YTUKy0tDWg
    0 Comments 0 Shares