0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
-
-
-
በቁም እንስሳት ላይ የሚፈፀምን የኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል ለአርብቶ አደሩ ምቹ የገበያ ሁኔታ ሊፈጠርለት ይገባል ተባለ።
ኢትዮጵያ በቁም እንስሳት ሀብቷ ከአፍሪካ በቀዳሚነት የምትገኝ ሲሆን፥ በዓለምም በዘርፉ ሰፊ ሀብት ካላቸው ጥቂት ሀገራት ተርታ ትመደባለች።
ይሁን እንጂ ይኸው ሀብቷ ለደላሎች እና ለህገወጥ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሲሳይ እየሆነ የሀብቷን ያህል መጠቀም ሳትችል የበይ ተመልካች በመሆን ብቻ ዓመታት ተቆጥረዋል።
በእንስሳት እና አሳ ሀብት ልማት ሚንስቴር የእንስሳት እና የእንስሳት ምርት ዳይሬክተሩ አቶ ፍቃዱ ጌታቸው እንደሚናገሩት፥ ህገወጥ የንግድ ሰንሰለቱ በሀገሪቱ ስር የሰደደ ነው።
በዚህም የቁም እንስሳት የኮንትሮባንድ ንግድ አሁን ላይ በመላ ሀገሪቱ የሚከናወን ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ሱማሌ፣ አፋር እና ቤንሻንጉልጉሙዝ፣ ትግራይ እና ኦሮሚያ ክልሎች ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ።
በጎዴ፣ ቶጎ ጫሌ እና በባሌ አካባቢዎች ህገወጥ ደላሎቹ በስፋት የሚንቀሳቀሱበት ስፍራዎችም ሆነው ተለይተዋል።
በሀገር ደረጃ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመቆጣጠር ግብረ ሀይል የተቋቋመ ሲሆን፥ የአሳ እና እንስሳት ሀብት ልማት ሚንስቴር ችግሩን በጥናት መለየቱን ለማወቅ ችለናል።
እንሰሳቱን ከሀገር ለማስወጣት በሚደረገው ጥረት ውስጥ በፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር ሲውሉ የመኖ፣ የጥበቃ፣ የህክምና እና የመሳሰሉት አገልግሎቶችን ለሟሟላት የሚያስችል በጀት ባለመኖሩ እርምጃ ለመውሰድ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ፈጥሯል።
ይህንን ችግር በጥናት በመለየትም ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ አዲስ ስልት ቀይሷል።
ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ የቁጥጥር ሂደቱን ህጋዊ ለማድረግ በህገወጥ መንገድ የሚያዙት እንስሳቶች በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ህጋዊ ግብይት ተፈጽሞ የሚመለስ 30 ሚልየን ብር በጀት ለማስፀደቅ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን አቶ ፈቃዱ ተናግረዋል።
ከዚህ እንቅስቃሴ ጎን ለጎንም ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ስጋ እና ወተት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በቅንጅት አርብቶ አደሩን ከህገወጥ ደላሎች ለመነጠልና ረዥም የግብይት ሰንሰለቱን ለማሳጠር እየሰሩ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል።
በኢትዮጵያ ስጋ እና ወተት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የስጋ፣ የማርና መኖ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ አስተባባሪ ዶክተር ተቀባ እሸቴ፥ ኢንስቲትዩቱ አርሶ አደሩን እና ህጋዊ ነጋዴውን ለማቀራረብ እየሰራ እንደሆነ ነው የተናገሩት።
በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ ያሉት ቄራዎች 57 ሺህ ቶን ስጋ በዓመት እያመረቱ ለዓለም አቀፍ ገበያ አያቀረቡ ነው።
በቅርቡ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ የሚጠበቀው “አላና ኢንድያ” የተሰኘው ግዙፍ የቄራ ፋብሪካ ብቻውን ደግሞ 130 ሺህ ቶን የስጋ ምርት ማምረት የሚያስችል አቅም ይዞ ገበያው ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።
እነዚህ ሁኔታዎችም ለአርብቶ አደሩ ምቹ የገበያ አማራጮችን በመፍጠር ተጠቃሚነትን ያረጋግጣሉ ተብሎም በመንግስት ታምኖበታል።
የቁም እንስሳት ግብይትን ዘመናዊ እና ቀልጣፋ ለማድረግ በ2006 ዓ.ም ዘመናዊ የግብይት ስርዓት አዋጅ ወጥቶ ተግባራዊ ሆኗል።
የአዋጁ መተግበር ወጣቶች ተደራጅተው በከብት ማድለብ እንዲሰማሩ እና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ያስቻለ ቢሆንም፥ አርኪ በሚባል ደረጃ ግን አለመተግበሩን ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ማሳያ ናቸው።በቁም እንስሳት ላይ የሚፈፀምን የኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል ለአርብቶ አደሩ ምቹ የገበያ ሁኔታ ሊፈጠርለት ይገባል ተባለ። ኢትዮጵያ በቁም እንስሳት ሀብቷ ከአፍሪካ በቀዳሚነት የምትገኝ ሲሆን፥ በዓለምም በዘርፉ ሰፊ ሀብት ካላቸው ጥቂት ሀገራት ተርታ ትመደባለች። ይሁን እንጂ ይኸው ሀብቷ ለደላሎች እና ለህገወጥ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሲሳይ እየሆነ የሀብቷን ያህል መጠቀም ሳትችል የበይ ተመልካች በመሆን ብቻ ዓመታት ተቆጥረዋል። በእንስሳት እና አሳ ሀብት ልማት ሚንስቴር የእንስሳት እና የእንስሳት ምርት ዳይሬክተሩ አቶ ፍቃዱ ጌታቸው እንደሚናገሩት፥ ህገወጥ የንግድ ሰንሰለቱ በሀገሪቱ ስር የሰደደ ነው። በዚህም የቁም እንስሳት የኮንትሮባንድ ንግድ አሁን ላይ በመላ ሀገሪቱ የሚከናወን ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ሱማሌ፣ አፋር እና ቤንሻንጉልጉሙዝ፣ ትግራይ እና ኦሮሚያ ክልሎች ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ። በጎዴ፣ ቶጎ ጫሌ እና በባሌ አካባቢዎች ህገወጥ ደላሎቹ በስፋት የሚንቀሳቀሱበት ስፍራዎችም ሆነው ተለይተዋል። በሀገር ደረጃ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመቆጣጠር ግብረ ሀይል የተቋቋመ ሲሆን፥ የአሳ እና እንስሳት ሀብት ልማት ሚንስቴር ችግሩን በጥናት መለየቱን ለማወቅ ችለናል። እንሰሳቱን ከሀገር ለማስወጣት በሚደረገው ጥረት ውስጥ በፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር ሲውሉ የመኖ፣ የጥበቃ፣ የህክምና እና የመሳሰሉት አገልግሎቶችን ለሟሟላት የሚያስችል በጀት ባለመኖሩ እርምጃ ለመውሰድ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። ይህንን ችግር በጥናት በመለየትም ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ አዲስ ስልት ቀይሷል። ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ የቁጥጥር ሂደቱን ህጋዊ ለማድረግ በህገወጥ መንገድ የሚያዙት እንስሳቶች በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ህጋዊ ግብይት ተፈጽሞ የሚመለስ 30 ሚልየን ብር በጀት ለማስፀደቅ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን አቶ ፈቃዱ ተናግረዋል። ከዚህ እንቅስቃሴ ጎን ለጎንም ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ስጋ እና ወተት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በቅንጅት አርብቶ አደሩን ከህገወጥ ደላሎች ለመነጠልና ረዥም የግብይት ሰንሰለቱን ለማሳጠር እየሰሩ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል። በኢትዮጵያ ስጋ እና ወተት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የስጋ፣ የማርና መኖ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ አስተባባሪ ዶክተር ተቀባ እሸቴ፥ ኢንስቲትዩቱ አርሶ አደሩን እና ህጋዊ ነጋዴውን ለማቀራረብ እየሰራ እንደሆነ ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ ያሉት ቄራዎች 57 ሺህ ቶን ስጋ በዓመት እያመረቱ ለዓለም አቀፍ ገበያ አያቀረቡ ነው። በቅርቡ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ የሚጠበቀው “አላና ኢንድያ” የተሰኘው ግዙፍ የቄራ ፋብሪካ ብቻውን ደግሞ 130 ሺህ ቶን የስጋ ምርት ማምረት የሚያስችል አቅም ይዞ ገበያው ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል። እነዚህ ሁኔታዎችም ለአርብቶ አደሩ ምቹ የገበያ አማራጮችን በመፍጠር ተጠቃሚነትን ያረጋግጣሉ ተብሎም በመንግስት ታምኖበታል። የቁም እንስሳት ግብይትን ዘመናዊ እና ቀልጣፋ ለማድረግ በ2006 ዓ.ም ዘመናዊ የግብይት ስርዓት አዋጅ ወጥቶ ተግባራዊ ሆኗል። የአዋጁ መተግበር ወጣቶች ተደራጅተው በከብት ማድለብ እንዲሰማሩ እና የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ያስቻለ ቢሆንም፥ አርኪ በሚባል ደረጃ ግን አለመተግበሩን ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ማሳያ ናቸው። -
https://www.youtube.com/watch?v=rPQQTr1LGvk
-
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእንግሊዝ ሊያደርጉት የነበረውን ጉብኝት መሰረዛቸው አስታውቀዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፊታችን የካቲት ለመማድረግ በነበረው ጉብኝት በለንደን ከተማ በ1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተገነባውን አዲሱን የአሜሪካ ኤምባሲ መርቀው እንደሚከፍቱ ይጠበቅ ነበር።
ፕሬዚዳንቱ በትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍም፥ “ከለንደን ሜይፌይር ወደ ደቡብ ለንደን የተቀየረውን አዲሱን ኤምባሲ ብዙም አልወደድኩትም” ብለዋል።
“የቀድሞ ኤምባሲ በቀድሞ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለማይረባ ነገር ተሸጧል” ሲሉም ፕሬዚዳንቱ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
ፕሬዚዳንቱ የፊታችን የካቲት ወር በለንደን ሊያካሂዱት አስበው የነበረው ጉብኝት በእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ የቀረበ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እንዳልነበረም ተነግሯል።
የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝትን መሰረዝ ላይ የእንግሊዝ መንግስት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል።
ፕሬዚዳንቱ ለመቅረታቸው ኤምባሲውን መክፈት ስለማይፈልጉ መሆኑን ቢጠቅሱም፤ በለንደን አውራ ጎዳናዎች ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ሊደርስባቸው ይችላል በሚል ስጋት ጉብኝቱ ሳይሰረዝ እንዳልቀረ ነው እየተነገረ ያለው።
የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የየካቲት ወር ጉብኝት መርሃ ግብር ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ ጋር መወያየት እና ከእንግሊዟ ንግስት ጋር ምሳ መብላት ተካቶበት እንደበረም ተነግሯል።
ዶናልድ ትራምፕ ኤምባሲውን ለመመረቅ ፍቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የኤምባሲውን ሪባን ቆርጠው ሊመርቁ ይችላሉ ተብሏል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ዓመት ከእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ ጋር ተገናኝተው በተወያዩበት ወቅት ነበር ከእንግሊዟ ንግስት የቀረበላቸውን ግብዣ የተቀበሉት።
ይህንን ተከትሎም 1 ነጥብ 8 ሚሊየን እንግሊዛውያን ፕሬዚዳንቱ እንግሊዝን መጎብኘት የለባቸውም የሚለው የፊርማ ማሰባሰብ ላይ ፈርመው የነበረ ሲሆን፥ ጉዳዩም ለሀገሩቱ ፓርላማ ቀርቦ ክርክር ተካሂዶበት እንደነበረ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ቢቢሲየአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእንግሊዝ ሊያደርጉት የነበረውን ጉብኝት መሰረዛቸው አስታውቀዋል። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፊታችን የካቲት ለመማድረግ በነበረው ጉብኝት በለንደን ከተማ በ1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተገነባውን አዲሱን የአሜሪካ ኤምባሲ መርቀው እንደሚከፍቱ ይጠበቅ ነበር። ፕሬዚዳንቱ በትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍም፥ “ከለንደን ሜይፌይር ወደ ደቡብ ለንደን የተቀየረውን አዲሱን ኤምባሲ ብዙም አልወደድኩትም” ብለዋል። “የቀድሞ ኤምባሲ በቀድሞ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለማይረባ ነገር ተሸጧል” ሲሉም ፕሬዚዳንቱ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። ፕሬዚዳንቱ የፊታችን የካቲት ወር በለንደን ሊያካሂዱት አስበው የነበረው ጉብኝት በእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ የቀረበ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እንዳልነበረም ተነግሯል። የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጉብኝትን መሰረዝ ላይ የእንግሊዝ መንግስት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል። ፕሬዚዳንቱ ለመቅረታቸው ኤምባሲውን መክፈት ስለማይፈልጉ መሆኑን ቢጠቅሱም፤ በለንደን አውራ ጎዳናዎች ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ሊደርስባቸው ይችላል በሚል ስጋት ጉብኝቱ ሳይሰረዝ እንዳልቀረ ነው እየተነገረ ያለው። የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የየካቲት ወር ጉብኝት መርሃ ግብር ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ ጋር መወያየት እና ከእንግሊዟ ንግስት ጋር ምሳ መብላት ተካቶበት እንደበረም ተነግሯል። ዶናልድ ትራምፕ ኤምባሲውን ለመመረቅ ፍቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የኤምባሲውን ሪባን ቆርጠው ሊመርቁ ይችላሉ ተብሏል። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ዓመት ከእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቴሬዛ ሜይ ጋር ተገናኝተው በተወያዩበት ወቅት ነበር ከእንግሊዟ ንግስት የቀረበላቸውን ግብዣ የተቀበሉት። ይህንን ተከትሎም 1 ነጥብ 8 ሚሊየን እንግሊዛውያን ፕሬዚዳንቱ እንግሊዝን መጎብኘት የለባቸውም የሚለው የፊርማ ማሰባሰብ ላይ ፈርመው የነበረ ሲሆን፥ ጉዳዩም ለሀገሩቱ ፓርላማ ቀርቦ ክርክር ተካሂዶበት እንደነበረ ይታወሳል። ምንጭ፦ ቢቢሲ -
https://reliefweb.int/report/ethiopia/ethiopia-food-assistance-fact-sheet-updated-january-5-2018RELIEFWEB.INTEthiopia: Food Assistance Fact Sheet - Updated January 5, 2018News and Press Release from US Agency for International Development, published 08 Jan 2018