• AMHARIC.VOANEWS.COM
    ጉባኤ ያካሄደው ህወሓት አቶ ጌታቸውን ጨምሮ 16 አመራሮችን ከፓርቲው ማባረሩን ገለፀ
    በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ቡድን ባካሄደው ጉባኤ የተመረጠው አዲሱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 16 አመራሮቹን ከፓርቲው ማባረሩን እና ፖለቲካዊ ስራዎች እንዳይከውኑ ማገዱን አስታወቀ፡፡ በተጨማሪም በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ኃላፊነት ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ እንደሚፈልግ ገልጿል። ታግደዋል ከተባሉ አንዱ እና የክልሉ የኮምዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ረዳኢ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    በምስራቅ ወለጋ በተፈፀመ ጥቃት ሁለት የቀበሌ ተሹዋሚዎች ተገደሉ
    ባለፈዉ ቅዳሜ በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ ተፈፀመ በተባለ ጥቃት ሁለት የቀበሌ አስተዳደር ሹሞች መቁሰላቸዉ ተዘግቦአል። ከኪረሙ ወረዳ አስተዳደር በቅርብ በተዋቀረዉ የቀበሌ መስተዳደር ወደ ስሬ ዶሮ ቀበሌ በሞተር ብስክሌት ሲጉዋዙ ከነበሩ ሰዎች የስሬ ዶሮ አስተዳዳሪ እና የቀበሌዉ የቀበሌዉ የፓርቲ ፅህፈት ቤት አስተባባሪ ወድያዉ መገደላቸዉን የተጎጂ ቤተሰቦች ና ከጥቃቱ የተረፉ የአይን እማኝ ተናግረዋል። የአካባቢው የመንግስት ባልደረባም ስለ ጥቃቱ ተናግረዋል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    አሜሪካ ወታደሮቿን ሙሉ ለሙሉ ከኒጀር አስወጣች
    አሜሪካ ወታደሮቿን ከኒጀር አስወጥታ ማጠናቀቋን አንድ ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣን ትላንት ሰኞ አስታውቀዋል፡ የፔንታገን ቃል አቀባይ የሆኑት ሳብሪና ሲንግ፣ በኒጀር የሚገኘውን የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ለመጠበቅ ጥቂት ወታደሮች ብቻ መቅረታቸውንም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ በአውሮፓዊያኑ 2024 መግቢያ ላይ፣ የኒጀር ወታደራዊ ጁንታ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በምዕራባዊቷ አፍሪካ ሃገር ያላቸውን ተልዕኮ የፈቀደውን ስምምነት እንዲያበቃ አድርጓል፡፡...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    በሊባኖስ ተንቀሳቃሽ የመልዕክት መቀበያዎች ፈንድተው ዘጠኝ ሰዎች ሞቱ፣ ብዙዎች ተጎዱ
    ከቤሩት ከተማ ዳርቻና በሌሎችም የሌባኖስ ክፍሎች የሚገኙ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የተንቀሳቃሽ መልዕክት መቀበያ መሳሪውያዎች (ፔጀሮች) ፈንድተው ዘጠኝ ሰዎች ሲሞቱ፣ በመቶ የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው የሊባኖስ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እና የደህንነት ኃላፊዎች አስታወቁ፡፡ አንድ የሊባኖስ ከፍተኛ የወታደራዊና ደህነንት ባለስልጣን እና ሌላ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ግለሰብ፤ ከሁኔታው አሳሳቢነት አንጻር ማንነታቸው እንዳይገልጽ ጠይቀው አስተያየታቸውን...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የአማጺያን ጥቃት የደረሰባት ማሊ መዲናዋን መቆጣጠሯን አስታወቀች
    ማሊ ዛሬ ንጋት ላይ አማጺያን በፖሊስ ማሰልጠኛና ሌሎችም ሥፍራዎች ላይ ያደረሱትን ጥቃትና የተኩስ እሩምታ ተከትሉ፣ መዲናዋን ባማኮ በቁጥጥር ስር ማድረጉን መንግስት አስታውቋል። “ንጋት ላይ የሽብር ቡድኖች ፋላዴ የፖሊስ ማሰልጠኛን ሊቆጣጠሩ ሞክረው ነበር” ያለው ሰራዊቱ፤ አያይዞም፣ “በአሁን ሰዓት የተቀሩትን የማጽዳት ስራ እየተካሄደ ነው” ሲል በመግለጫው አስታውቋል፡፡ ይፋዊ ተጨማሪ መግለጫ እስኪሰጥ ድረስም ነዋሪዎች ከአካባቢው እንዲርቁ ጥሪ ተደርጓል፡፡...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አረፉ
    ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በ75 ዓመታቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በፖለቲካ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ከቆዩ አንጋፋ የፖለቲካ ሰዎች መካከል አንዱ መሆናቸው የሚነገርላቸው በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር)÷ የተፎካካሪ ፓርቲው የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ነበሩ፡፡ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በበየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) ሕልፈተ-ሕይወት የተሰማውን ሐዘን ገልፆ ኢትዮጵያ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ትረምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ከተቃጣባቸው የግድያ ሙከራ ተረፉ
    እንደ ባለሥልጣናቱ ገለጣ ዶናልድ ትረምፕ በሁለት ወራት ዕድሜው ለሁለተኛ ዙር ከተቃጣባቸው ያልተሳካ የግድያ ሙከራ ተርፈዋል። በትላንትናው ዕለት የተፈጸመው እና ተጠርጣሪ በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ሥር የዋለበት ምርመራ ሂደት በፌድራሉ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኤፍቢአይ መሪነት እየተካሄደ መሆኑም ተገልጿል። ድንገቱ ቀድሞውንም ከፍተኛ ትኩረት በሳበው እና ባልተጠበቁ አስገራሚ እንቅስቃሴዎች በተመላው የምርጫ ሂደት፤ አሜሪካውያን ሌላ ያልተጠበቀ ሁኔታ ገጥሟቸዋል። የአሜሪካ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የትግራይ ፀጥታ ሓይሎች ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠቡ የክልሉ ፓርቲዎች ጠየቁ
    የትግራይ ክልል የፀጥታ ሓይሎች በክልሉ ፖለቲካ ጣልቃ እየገቡ በመሆናቸው ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሲሉ አራት የክልሉ ፓርቲዎች ጠየቁ:: ፓርቲዎቹ፣ ብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና)፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ ውድብ ናፅነት ትግራይ እንዲሁም ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲ እና ሉዕላውነት ይህን የጠየቁት በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው፡፡ በመግለጫቸውም በክልሉ ሰልፍ የሚከለክል ጥሪ በአዋጅ እና በሕግ ያልተደገፈ ነው ሲሉ ተቃውመዋል:: ትናንት እሁድ የክልሉ...
    0 Comments 0 Shares