0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMየተራዘመው የጠፈር ጉዞለአንድ ሳምንት ቆይታ ወደ ሕዋ የተጓዙት ባለሙያዎች፣ ለምን ለወራት ሳይመለሱ ቀሩ? የዘጠኝ ቀናት ያህል ቆይታ ለማድረግ ‘ቦይንግ ስታርላይነር’ በተሰኘችው መንኮራኩር ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ሕዋው የመጠቁት የጠፈር ሳይንስ ባለሙያው ቤሪ ዊልሞር እና ሴቷ የጠፈር ባለሙያ ሱኒ ዊሊያምስ፣ መንኮራኩሯ እክል ስለገጠማት ቢያንስ ለስምንት ወራት ለመቆየት እንደሚገደዱ ታውቋል። ባለሙያዎቹ በዓለም ዓቀፉ የሕዋ ጣቢያ ካሉና ምድርን ከለቀቁ ከረምረም ያሉ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMሺ ጂንፒንግ ለአፍሪካ የ50.7 ቢሊዮን ዶላር መደቡየቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ሀገራቸው ለአፍሪካ 50.7 ቢሊዮን ዶላር እንደምትሰጥ ቃል ገብተዋል። ከዚህም ውስጥ፣ 11 ቢሊዮን ዶላር በብድር መልክ የሚሰጥ ሲሆን 10 ቢሊዮን ዶላር በአፍሪካ የቻይናን ኢንቨስትመንት ለማበረታታት እንደሚውል ተገልጿል። ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምጽ ማጫወቻ ያድምጡ፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMዩናይትድ ስቴትስ ከሞስኮ ጋራ ግንኙነት ባላቸው ኩባንያዎችና ሠራተኞቻቸው ላይ ማዕቀብ ጣለችሩሲያ፤ በአሜሪካ ማኅበረሰብ ላይና በመጪው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ውጤት ላይ ተጽእኖ ለማሳደር፣ አደገኛ የሃሰት መረጃ የማሰራጨት ዘመቻ በማድረግ ላይ ነች በሚል፣ የአሜሪካ መንግስት ትላንት ረቡዕ ከሞስኮ ጋራ ግንኙነት ባላቸው ኩባንያዎችና ሠራተኞቻቸው ላይ ክስ መስርቶ ማዕቀብ ጥሏል። ሌሎችንም እርምጃዎችን መውሰዱንም አስታውቋል። በአሜሪካ የፍትህ እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም ዋናው ግምጃ ቤት በጋራ እንዳስታወቁት፣ ሩሲያ፣ የፕሬዝደንት ቭላድሚር...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ፣ በየሦስት ወሩ ሊጨመር ነውመንግሥታዊው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ በየሶስት ወሩ፣ በአገልግሎት ክፍያ ላይ ጭማሪ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ፣ በትላንትናው ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ አዲሱ የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት እንደሚቆይ ተናግረዋል፡፡ በክፍያ ማስተካከያው፣ ከ50 እስከ 200 ኪሎዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀሙ አብዛኞቹ ደንበኞች ድጎማ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየኦሮሚያ ክልል መንግሥትና ኦፌኮ በቀበሌ አደረጃጀት ጉዳይ የተለያየ አቋም ይዘዋልየቀበሌ አስተዳደር መዋቅሮችን መልሶ ማዋቀሩን ያስታወቀው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት፣ የመዋቅሩ አላማም የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል መሆኑን አመልክቷል። የክልሉ የሕበረተሰብ አገልግሎት እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ኮከበ ዲዳ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ አዲሱ አወቃቀር ለቀበሌዎች ከቀድሞው የተሻለ ኃላፊነት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በክልሉ የሚገኙ ከሰባት ሽህ በላይ ቀበሌዎች በአዲስ መልክ መዋቀራቸው፣ በአብዛኛው በወረዳዎች ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMሰዎች "በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው" ሲሉ በደራሼ ልዩ ወረዳ የሚገኙ የቤተሰብ አባላት አማረሩበደቡብ ኢትዮጵያ ክል፣ ጋርዱላ ዞን፣ ደራሼ ወረዳ፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችንና የማሕበረሰባዊ ፖሊሰ አባላትን ጨምሮ 21 ሰዎች “ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በዘፈቀደ ታስረዋል” ሲሉ ቤተሰቦቻቸውና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ መጀመሪያ ከታሰሩበት የዞኑ ዋና ከተማ ጊዶሌ ወደ ሌላ አከባቢ መወሰዳቸውን የጠቀሱት የቤተሰብ አባላት የደህንነተቸው ጉዳይ እንደሚያሳስባቸውም ተናገረዋል። ‘በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ታስረዋል’ ያለው የጋርዱላ ዞን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበዩናይትድ ስቴትስ ጆርጂያ ግዛት የ14 ዓመት ታዳጊ አራት ሰዎችን በመግደል ተከሰሰበዩናይትድ ስቴትስ ጆርጂያ ግዛት፣ ከአትላንታ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አፓላቺ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት የ14 ዓመት ተማሪዎችን እና ሁለት መምህራንን የገደለው ታዳጊ በግድያ ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል። ታዳጊው ትላንት ረቡዕ በትምህርት ቤቱ ውስጥ በተከፈተው ተኩስ ሌሎች ስምንት ተማሪዎች እና አንድ አስተማሪ ማቁሰሉንም ባለስልጣናት ገልጸዋል። ከአንድ ዓመት በፊት በትምህርት ቤት ላይ ተኩስ እንደሚከፍት በመዛት በድረ-ገጾች ላይ ይፅፍ እንደነበር...0 Comments 0 Shares