0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበአፍሪካ ለኤምፖክስ የተጋለጡ ወደ 4ሺ ሰዎች ተመዘገቡየአፍሪካ የበሽታ መከላከልና ቁጥጥር ማዕከል ባለፈው ሳምንት በአህጉሪቱ ወደ 4,000 የሚጠጉ ለኤምፖክስ የተጋለጡ አዳዲስ ሰዎች መመዝገባቸውና ወረረሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን አስታወቀ፡፡ ማዕከሉ በወረረሽኙ እጅግ ወደተጎዳችው ኮንጎ የተላከው የመጀመሪያው ዙር ክትባት በመዘግየቱ አስፈላጊ ክትባቶች በአፋጣኝ እንዲሰጡ በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ በአፍሪካ ባለፈው ሳምንት ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ 81 ሰዎች ሞተዋል፡፡ ይህ ቀደም ሲል የነበረውን የሟቾች ቁጥር...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMቱኒዚያ ህገወጥ የፍልስተኞች ጀልባ ሠርቷል ያለችውን ጣሊያናዊ ያዘችየቱኒዚያ ባለሥልጣናት ወደ አውሮፓ ለመግባት የሚሞክሩ ህገወጥ ፍልሰተኞች የሚጠቀሙበትን ጀልባ በመስራት የተጠረጠረውን የ45 ዓመቱን ጣሊያናዊ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡ ግለሰቡ በጀልባ ግንባታ ፋብሪካ ውስጥ የሚሠራ መሆኑን በምስራቅ ቱኒዝያ የምትገኘው የሞናስቲር ከተማ አቃቤ ህግ ቃል አቀባይ ፋሪድ ጃሃ ተናግረዋል። ከሜዲትሬኒያን ባህር ወደ አውሮፓ እንዲያሻግር ከፕላስቲክ የተሰራውን ጀልባ ግንባታ በማቀድ የተሳተፉ ሶስት ቱኒዚያውያንም...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMመንግሥት 50 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባ መሆኑን አስታወቀመንግሥት የኑሮ ውድነትን የማሻሻል እርምጃ አካል በማድረግ 50 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ አያስገባ መሆኑን አስታውቋል አስተያየታቸውን የሰጡን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ መንግሥት እርምጃ መውሰድ ከጀመረ በኋላ በዘይት ላይ የተወሰነ የዋጋ መሻሻል መኖሩን ገልጸው፣ ኾኖም የዋጋ ንረቱ ፈታኝ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡ የምጣኔ ኃብት ተንታኝ የኾኑት አቶ አማንይሁን ረዳ፣ በሀገር ውስጥ በበቂ መጠን ማምረት እስኪቻል ድረስ፣ የኑሮ ውድነት ጫናን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደለችው ሄቨን ፍትህ ለመጠየቅ የሚደረጉ ጥረቶች ቀጥለዋልበአሰቃዊ ሁኔታ ተደፍራ ለተገደለችው ህጻን ሄቨን አወት የተለያዩ አካላት ፍትህ መጠየቃቸውን የቀጠሉ ሲሆን አርብ እለት አዲስ አበባ በሚገኘው ኢሊሌ ሆቴል ሊደረግ የነበረው እና በጸጥታ አካላት እንዲቋረጥ የተደረገውን ጋዜጣዊ መግለጫ እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር በድጋሚ ለማካሄድ ጥረት እየተደረገ ነው። የእናቶች ወግ ስለልጆች አስተዳደግ እና አመጋገብ የተሰኘው እና በፌስቡክ ላይ ከግማሽ ሚሊየን በላይ አባላት ያሉት ቡድን ቅዳሜ እለት ባካሄደው የደም ልገሳ ፕሮግራም...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMዩክሬን የሩሲያን የኩርስክ ግዛት መጠነ ሠፊ ሥፍራ ተቆጣጠርኩ አለችየዩክሬን ጦር አዛዥ በዛሬው ዕለት በሰጡት አስተያየት የኪየቭ ኃይሎች ባለፉት ሶስት ሳምንታት ባካሄዱት ወታደራዊ ዘመቻ 1,300 ካሬ ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የሩሲያ ኩርስክ ግዛት መቆጣጠራቸውን እና በሩስያ ኅያሎች ተይዘው የሚገኙ ዩክሬይናውያንን ለማስለቀቂያ ያሰቧቸውን 594 ሩስያውያን መማረካቸውን ተናግረዋል። ጄኔራል ኦሌክሳንደር ሲርስኪ ሲናገሩ፤ በዩክሬን ጦር ግስጋሴ የተነሳ “የጥቃት እርምጃ እየፈጸመ ባለው ኃይላችን ዙሪያ የመከላከያ ቀለበት ለማበጀት እና...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየአቪዬሸን አሰራርን በመጣስ የተጠረጠሩ 6 ሰዎች ፍርድ ቤት ቀረቡባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 16 ቀን ከአዲስ አበባ መቀሌ ጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በመፍጠር የተጠረጠሩ ስድስት ተከሳሾች፣ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ቀርበዋል። ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች አንዷ ጀሚላ መስፍን ለአሜሪካ ድምጽ እንደገለፁት፣ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን የዋስትና ጥያቄ ባለመቀበል፣ የፌደራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። የፌዴሬል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMእስያ አሜሪካውያን ድምጽ ሰጪዎች በባህላቸውም፣ በፖለቲካ አመለካከታቸውም የተለያዩ ናቸው‘ ፒው የምርምር ማዕከል’ የተሰኘው ተቋም እንደሚለው፣ ከእ.አ.አ 2020 ዓ/ም ወዲህ እስያ አሜሪካውያን በአሜሪካ ቁራቸው እጅግ በፍጥነት እያደገ የመጣ ድምፅ ሰጪዎችን የያዘ ማኅበረሰብ ሆኗል። በ2022 ዓ/ም የካልፎርኒያ ግዛት በአሜሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የእስያ ማኅበረሰብ ዓባላት ሲይዝ፣ ኒው ዮርክና ቴክሳስ ደግሞ ይከተላሉ። የቪኦኤዋ ኤሊዛቤት ሊ ከሂውስተን ቴክሳስ በላከችው ዘገባ የእስያ አሜሪካውያን ድምፅ ሰጪዎች ሊኖራቸው የሚችለውን አቅምና...0 Comments 0 Shares