• Ethiopia Unblocks 264 Websites and TV Channels, Ginbot 7 Suspends Armed Resistance (BBC)
    Ethiopia Unblocks 264 Websites and TV Channels, Ginbot 7 Suspends Armed Resistance (BBC)
    0 Comments 0 Shares
  • ጠ/ሚኒስትሩ ወደ አስመራ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተጠቆመ   ላለፉት 10 ዓመታት የትጥቅ ትግልን ጨምሮ ማንኛውንም የትግል ስልት አማራጭ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው አርበኞች ግንቦት 7፤ ከትላንት ሰኔ 15 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የአመፅና የትጥቅ እንቅስቃሴ ማቆሙን አስታውቋል፡፡“በሃገራችን የዲሞክራሲ ለውጥ ለማምጣት ተገደን የገባንበት ማንኛውንም ሰላማዊ ያልሆነ እንቅስቃሴ ገተናል” ያለው ንቅናቄው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ የሚመሩት የለውጥ ሂደት፤ ተስፋ ፈንጣቂና አበረታች በመሆኑ፣ ልዩ ስብሰባ በማድረግ፣ የትጥቅና የአመፅ ትግሉን ለማቆም መወሠኑን ገልጿል፡፡ከትናንት ጀምሮም በኢትዮጵያ ምንም አይነት አመፅ ነክ እንቅስቃሴ ከማድረግ መቆጠቡን ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል፡፡  የሃገሪቱን የወሠንና የክልል አስተዳደር ለማስተካከል ሊዋቀር በታሰበው ኮሚሽን ውስጥ ተሣትፎ በማድረግ አስተዋፅኦ ለማበርከት ፍላጎት እንዳለው ያስታወቀው ንቅናቄው፤ “ዶ/ር አብይ የትግራይ ህዝብንና ህወሓትን ለያይቶ መመልከት እንደሚገባ ያሳሰቡትን ሃቅ፤ እኛም የምንጋራው ነው” ብሏል፡፡ በአገሪቱ አዲስ የተጀመረው ለውጥ በአሻጥር እንዳይቀለበስ፣ አርበኞች ግንቦት 7 ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎን እንደሚሠለፍም በመግለጫው አቋሙን ገልጿል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትን ተከትሎ፣ ለሁለት አስርት ዓመታት በሁለቱ አገራት መካከል የዘለቀውን ፍጥጫ በማስቆም ግንኙነታቸውን ለማሻሻል የተጀመረው ጥረት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አድናቆትና ድጋፍ እየተቸረለት ነው፡፡ “ለ20 ዓመታት የዘለቀው ፍጥጫ የሚያበቃበት ምዕራፍ ተጀምሯል” ብለዋል-በጃፓን የኤርትራ አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂ፡፡የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ በበኩላቸው፤ በኤርትራ በየዓመቱ ሰኔ 13 በሚከበረው የሰማዕታት ቀን በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የሰላም ጥሪውን እንደሚቀበሉ ጠቁመው፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚነጋገር የልኡካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚልኩ አስታውቀዋል፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፤ ከኤርትራ በኩል በተገኘው ምላሽ መደሰታቸውን ጠቁመው፤ “በቀጣይ ለኤርትራና ለኢትዮጵያ ህዝቦች ተባብረን እንደምንሠራ እምነቴ ነው” ብለዋል፡፡ “የልኡካን ቡድኑን እንደ ኤርትራውያን ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያውያን በቢሮዬ ተቀብዬ በክብር አስተናግዳቸዋለሁ” ብለዋል፤ ጠ/ሚኒስትሩ በትግርኛ ቋንቋ በሰጡት ምላሽ፡፡የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በበኩሉ፤ የኤርትራ የልኡካንን ቡድን በታላቅ አክብሮት ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል። የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሰጡት ምላሽ፣ የክልላቸው ህዝብና መንግስት ልኡካኑን በአክብሮት ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሰሞኑን በወጣው ያልተረጋገጠ መረጃ፤ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ለመወያየት ወደ አስመራ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡
    ጠ/ሚኒስትሩ ወደ አስመራ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተጠቆመ   ላለፉት 10 ዓመታት የትጥቅ ትግልን ጨምሮ ማንኛውንም የትግል ስልት አማራጭ አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው አርበኞች ግንቦት 7፤ ከትላንት ሰኔ 15 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የአመፅና የትጥቅ እንቅስቃሴ ማቆሙን አስታውቋል፡፡“በሃገራችን የዲሞክራሲ ለውጥ ለማምጣት ተገደን የገባንበት ማንኛውንም ሰላማዊ ያልሆነ እንቅስቃሴ ገተናል” ያለው ንቅናቄው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ የሚመሩት የለውጥ ሂደት፤ ተስፋ ፈንጣቂና አበረታች በመሆኑ፣ ልዩ ስብሰባ በማድረግ፣ የትጥቅና የአመፅ ትግሉን ለማቆም መወሠኑን ገልጿል፡፡ከትናንት ጀምሮም በኢትዮጵያ ምንም አይነት አመፅ ነክ እንቅስቃሴ ከማድረግ መቆጠቡን ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል፡፡  የሃገሪቱን የወሠንና የክልል አስተዳደር ለማስተካከል ሊዋቀር በታሰበው ኮሚሽን ውስጥ ተሣትፎ በማድረግ አስተዋፅኦ ለማበርከት ፍላጎት እንዳለው ያስታወቀው ንቅናቄው፤ “ዶ/ር አብይ የትግራይ ህዝብንና ህወሓትን ለያይቶ መመልከት እንደሚገባ ያሳሰቡትን ሃቅ፤ እኛም የምንጋራው ነው” ብሏል፡፡ በአገሪቱ አዲስ የተጀመረው ለውጥ በአሻጥር እንዳይቀለበስ፣ አርበኞች ግንቦት 7 ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎን እንደሚሠለፍም በመግለጫው አቋሙን ገልጿል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትን ተከትሎ፣ ለሁለት አስርት ዓመታት በሁለቱ አገራት መካከል የዘለቀውን ፍጥጫ በማስቆም ግንኙነታቸውን ለማሻሻል የተጀመረው ጥረት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አድናቆትና ድጋፍ እየተቸረለት ነው፡፡ “ለ20 ዓመታት የዘለቀው ፍጥጫ የሚያበቃበት ምዕራፍ ተጀምሯል” ብለዋል-በጃፓን የኤርትራ አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂ፡፡የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ በበኩላቸው፤ በኤርትራ በየዓመቱ ሰኔ 13 በሚከበረው የሰማዕታት ቀን በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የሰላም ጥሪውን እንደሚቀበሉ ጠቁመው፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚነጋገር የልኡካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚልኩ አስታውቀዋል፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፤ ከኤርትራ በኩል በተገኘው ምላሽ መደሰታቸውን ጠቁመው፤ “በቀጣይ ለኤርትራና ለኢትዮጵያ ህዝቦች ተባብረን እንደምንሠራ እምነቴ ነው” ብለዋል፡፡ “የልኡካን ቡድኑን እንደ ኤርትራውያን ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያውያን በቢሮዬ ተቀብዬ በክብር አስተናግዳቸዋለሁ” ብለዋል፤ ጠ/ሚኒስትሩ በትግርኛ ቋንቋ በሰጡት ምላሽ፡፡የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በበኩሉ፤ የኤርትራ የልኡካንን ቡድን በታላቅ አክብሮት ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል። የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሰጡት ምላሽ፣ የክልላቸው ህዝብና መንግስት ልኡካኑን በአክብሮት ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሰሞኑን በወጣው ያልተረጋገጠ መረጃ፤ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ለመወያየት ወደ አስመራ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    “ግንቦት 7” ትግሉን ማቆሙን በይፋ አስታወቀ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">ጠ/ሚኒስትሩ ወደ አስመራ ሊጓዙ እንደሚችሉ ተጠቆመ<br /><br /> ላለፉት 10 ዓመታት የትጥቅ ትግልን ጨምሮ ማንኛውንም የትግል ስልት አማራ...
    0 Comments 0 Shares
  • ኦኤምኤን ቴሌቪዥን ዛሬ ከአዲስ አበባ ስርጭቱን ይጀምራል    መንግስት አገልግሎት እንዳይሰጡ ዘግቷቸው የነበሩ 264 የተለያዩ ድረ-ገጾችና የጦማርያን ገጾችን በመክፈት አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊው አቶ ፍጹም አረጋ ትናንት በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡በአሜሪካ ፍቃዱን አግኝቶ የሚሰራጨው የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) ቴሌቪዥን፣ በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ሥርጭቱን እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ማረጋገጥ፣ ለሌሎች መብቶች መከበር መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት አቶ ፍጹም፤ በመስኩ የማሻሻያ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ የሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት፣ ተዘግተው የነበሩ ድረ-ገጾችን በመክፈት፣ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን አመልክተዋል፡፡ነጻ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማድረግ፣ በአገሩ ጉዳይ ተሳታፊና ሃላፊነት የሚሰማው ዜጋ ለመፍጠር ቁልፍ ሚና ይጫወታል ያሉት አቶ ፍጹም፤ መንግስት የተዘጉ ድረገጾችን ከመክፈት በተጨማሪ የኢሳትና የኦኤምኤን የቴሌቪዥን ስርጭቶች በነጻነት እንዲታዩ መፍቀዱንም ገልጸዋል፡፡    አሶሼትድ ፕሬስ በበኩሉ፤ መንግስት ዘግቷቸው የነበሩት ብዙዎቹ ድረ-ገጾች በአሜሪካና በሌሎች ውጭ አገራት የተከፈቱ እንደሆኑ በመጠቆም፣ በአገሪቱ ታስረው የነበሩ ከሞላ ጎደል ሁሉም ጋዜጠኞችና ጦማሪያን በአዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ መንግስት ከእስር መለቀቃቸውንና መንግስትን በመተቸት በሚታወቁ አክቲቪስቶች ላይ ተመስርተው የነበሩ ክሶች መቋረጣቸውን ዘግቧል፡፡
    ኦኤምኤን ቴሌቪዥን ዛሬ ከአዲስ አበባ ስርጭቱን ይጀምራል    መንግስት አገልግሎት እንዳይሰጡ ዘግቷቸው የነበሩ 264 የተለያዩ ድረ-ገጾችና የጦማርያን ገጾችን በመክፈት አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊው አቶ ፍጹም አረጋ ትናንት በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡በአሜሪካ ፍቃዱን አግኝቶ የሚሰራጨው የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) ቴሌቪዥን፣ በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ሥርጭቱን እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ማረጋገጥ፣ ለሌሎች መብቶች መከበር መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት አቶ ፍጹም፤ በመስኩ የማሻሻያ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ የሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት፣ ተዘግተው የነበሩ ድረ-ገጾችን በመክፈት፣ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን አመልክተዋል፡፡ነጻ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማድረግ፣ በአገሩ ጉዳይ ተሳታፊና ሃላፊነት የሚሰማው ዜጋ ለመፍጠር ቁልፍ ሚና ይጫወታል ያሉት አቶ ፍጹም፤ መንግስት የተዘጉ ድረገጾችን ከመክፈት በተጨማሪ የኢሳትና የኦኤምኤን የቴሌቪዥን ስርጭቶች በነጻነት እንዲታዩ መፍቀዱንም ገልጸዋል፡፡    አሶሼትድ ፕሬስ በበኩሉ፤ መንግስት ዘግቷቸው የነበሩት ብዙዎቹ ድረ-ገጾች በአሜሪካና በሌሎች ውጭ አገራት የተከፈቱ እንደሆኑ በመጠቆም፣ በአገሪቱ ታስረው የነበሩ ከሞላ ጎደል ሁሉም ጋዜጠኞችና ጦማሪያን በአዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ መንግስት ከእስር መለቀቃቸውንና መንግስትን በመተቸት በሚታወቁ አክቲቪስቶች ላይ ተመስርተው የነበሩ ክሶች መቋረጣቸውን ዘግቧል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    መንግስት የዘጋቸውን 264 ድረ-ገጾች መክፈቱ ተነገረ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">ኦኤምኤን ቴሌቪዥን ዛሬ ከአዲስ አበባ ስርጭቱን ይጀምራል<br /><br /> መንግስት አገልግሎት እንዳይሰጡ ዘግቷቸው የነበሩ 264 የተለያዩ ድ...
    0 Comments 0 Shares
  •  በታሰሩ ግለሰቦች፤ በተፈናቀሉ ዜጎች፣ በፍትህ… ዙሪያ ውይይት ተደርጓል   የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አስፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ትናንት አርብ በባህር ዳር ተገኝተው፣ ከአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሠ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር በክልሉ የተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ገንቢ ውይይት ማድረጋቸው ተገለፀ፡፡ በዚህ የምስክር መድረክ ላይ በዋናነት በእስር ምክንያት ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መደበኛ የመንግስት ስራ በሚመለሡበት ሁኔታ፣ እስር ቤቶችን በመፈተሽ በእስር የተረሡ ወገኖች መልቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ አካሉ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ደብዛቸው የጠፋ ዜጎችና  24 አመት ሙሉ በእስር ላይ የሚገኙ የሃይማኖት ሊቅ በሚለቀቁበት ሁኔታ ላይም መወያየታቸውን የጠቆሙት ሃላፊው፤ የሠማያዊ ፓርቲ አባል የነበረውና ባልታወቁ ሠዎች የተገደለው ሣሙኤል አወቀ ጉዳይ ፍትህ እንዲያገኝም መግባባት ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም ከሌላ ክልል የተፈናቀሉ የክልሉ ተወላጆች በሚቋቋሙበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረናል ያሉት አቶ አበበ፤ ፓርቲው በአካባቢው በሚንቀሣቀሥበት ወቅት ወከባ እንዳይፈፀምበት ውጤታማ ምክክር መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
     በታሰሩ ግለሰቦች፤ በተፈናቀሉ ዜጎች፣ በፍትህ… ዙሪያ ውይይት ተደርጓል   የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አስፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ትናንት አርብ በባህር ዳር ተገኝተው፣ ከአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሠ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር በክልሉ የተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ገንቢ ውይይት ማድረጋቸው ተገለፀ፡፡ በዚህ የምስክር መድረክ ላይ በዋናነት በእስር ምክንያት ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መደበኛ የመንግስት ስራ በሚመለሡበት ሁኔታ፣ እስር ቤቶችን በመፈተሽ በእስር የተረሡ ወገኖች መልቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ አካሉ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ደብዛቸው የጠፋ ዜጎችና  24 አመት ሙሉ በእስር ላይ የሚገኙ የሃይማኖት ሊቅ በሚለቀቁበት ሁኔታ ላይም መወያየታቸውን የጠቆሙት ሃላፊው፤ የሠማያዊ ፓርቲ አባል የነበረውና ባልታወቁ ሠዎች የተገደለው ሣሙኤል አወቀ ጉዳይ ፍትህ እንዲያገኝም መግባባት ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም ከሌላ ክልል የተፈናቀሉ የክልሉ ተወላጆች በሚቋቋሙበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረናል ያሉት አቶ አበበ፤ ፓርቲው በአካባቢው በሚንቀሣቀሥበት ወቅት ወከባ እንዳይፈፀምበት ውጤታማ ምክክር መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የሠማያዊ ፓርቲ አመራሮች ከአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር ተመካከሩ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> በታሰሩ ግለሰቦች፤ በተፈናቀሉ ዜጎች፣ በፍትህ… ዙሪያ ውይይት ተደርጓል<br /><br /> የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አስፋን ጨም...
    0 Comments 0 Shares
  •  - ጠ/ሚኒስትሩ ህዝብ የሚያፈናቅሉ ከስልጣናቸው እንዲወርዱ አሳሰቡ   - ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ጉራጌ ዞን ራሣቸውን ችለው ክልል እንዲሆኑ ጥያቄ ቀርቧል     የወላይታ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን ሠሞኑን በአዋሣ በወላይታና በሲዳማ ብሄር ተወላጆች መካከል የተፈጠረውን ግጭት በፅኑ አውግዞ፣ አጥፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቋል፡፡ “ትርጉም አልባ ድርጊት” በማለት ግጭቱን ያወገዘው ፓርቲው፤ “ክስተቱ በወላይታና በሲዳማ ህዝብ መካከል ያለውን ወንድማማችነት የማይወክል ነው፤ ለወደፊቱ የሁለቱ ህዝቦች ወንድማማችነት እየተጠናከረ እንጂ እየላላ አይሄድም” ብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው በሃዋሳ እና በሶዶ ህዝቡን በማነጋገር ላደረጉት የማረጋጋት ስራ ምስጋናውን የገለፀው ፓርቲው፤ በሃገሪቱ የሚታዩ የብሄር ግጭቶች በመላው ህዝብ መወገዝ አለበት ብሏል፡፡ የወላይታ ህዝብ የሚተዳደርበት የግብርና ኢኮኖሚ አካባቢው ካለበት የመሬት ጥበትና የህዝብ ብዛት አንፃር እየተጣጣመ አለመምጣቱ፣ የአካባቢው ተወላጆች ስራ ፍለጋ ወደ ሌላ ቦታ እንዲንቀሣቀሱ ማስገደዱን የጠቆመው ፓርቲው፤ በቀጣይ በአካባቢው ያለው ፖሊሲ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ተኮር መሸጋገር እንደሚገባው ገልጿል፡፡ በወላይታ ለአንድ አርሶ አደር የሚደርሠው መሬት በአማካይ ከ0.13 ሄክታር በታች መሆኑን የጠቀሠው መግለጫው፤ በትንሹ ሶስት ልጆች ያሉት አባወራ፣ ቤተሠቡን መቀለብ እንኳ አይችልም ብሏል፡፡ ለዚህ መፍትሄው የወላይታ ህዝብ ራስን ችሎ በክልል እንዲተዳደር ማድረግና በአካባቢው ኢንዱስትሪ መር ፖሊሲን መተግበር ነው ብሏል፡፡ፓርቲው ግጭቱን ባወገዘበት መግለጫው፤ ህይወት ያጠፉ በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱና ሃብት ለወደመባቸው ተገቢ ካሣ እንዲከፈላቸው ጠይቋል፡፡ ከዚሁ ጉዳዩ ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፤ ከሠኞ እስከ ረቡዕ በሃዋሣ፣ በወላይታ ሶዶና በወልቂጤ ከተማ ባጋጠሙ ግጭቶች ላይ ከህዝብ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸው ወቅት ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል በሶስቱም ዞኖች “ራሳችንን ችለን ክልል እንሁን” የሚለው ይገኝበታል፡፡ በሲዳማ፣ በወላይታና በጉራጌ ማህበረሠቦች ራሣችን ችለን ክልል እንሁን የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄው ህጋዊ መሆኑን ጠቅሠው በቅርቡ አጠቃላይ የሃገሪቱ የወሠንና የክልሎችን ጉዳይ ፈትሾ፣ መፍትሄ የሚያበጀ ኮሚሽን ይቋቋማል ብለዋል።በየወረዳውና ዞኖቹ ግጭቶቹ ሲከሠቱና የሠው ህይወት ሲጠፋ በቸልታ የተመለከቱ አመራሮችም በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣን መልቀቅ እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሣስበዋል፡፡በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የአማራ ክልል ተወላጆችን ያፈናቀሉ ባለስልጣናትም ለህግ እንደሚቀርቡ የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የክልሉ ፕሬዚዳንት እኒህን አመራሮች ከስልጣን ያወርዳሉ ብለው እንደሚያምኑ አስታውቀዋል፡፡ ይህን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የስልጣን ልቀቁ ጥያቄ ተከትሎ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትላቸው ጨምሮ አምስት ከፍተኛ ባለስልጣናት በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣን ለቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ስልጣን መልቀቃቸው ተገቢ እና አርአያነት ያለው ነው ሌሎችም ይለቃሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል፡፡ሃዋሳ ላይ በተፈጠረው ግጭት 10 ሰዎች መሞታቸው እና በሺዎች መፈናቀላቸው እንዲሁም በወልቂጤ 5 ሰዎች መሞታቸው መገለፁ ይታወቃል፡፡
     - ጠ/ሚኒስትሩ ህዝብ የሚያፈናቅሉ ከስልጣናቸው እንዲወርዱ አሳሰቡ   - ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ጉራጌ ዞን ራሣቸውን ችለው ክልል እንዲሆኑ ጥያቄ ቀርቧል     የወላይታ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን ሠሞኑን በአዋሣ በወላይታና በሲዳማ ብሄር ተወላጆች መካከል የተፈጠረውን ግጭት በፅኑ አውግዞ፣ አጥፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቋል፡፡ “ትርጉም አልባ ድርጊት” በማለት ግጭቱን ያወገዘው ፓርቲው፤ “ክስተቱ በወላይታና በሲዳማ ህዝብ መካከል ያለውን ወንድማማችነት የማይወክል ነው፤ ለወደፊቱ የሁለቱ ህዝቦች ወንድማማችነት እየተጠናከረ እንጂ እየላላ አይሄድም” ብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው በሃዋሳ እና በሶዶ ህዝቡን በማነጋገር ላደረጉት የማረጋጋት ስራ ምስጋናውን የገለፀው ፓርቲው፤ በሃገሪቱ የሚታዩ የብሄር ግጭቶች በመላው ህዝብ መወገዝ አለበት ብሏል፡፡ የወላይታ ህዝብ የሚተዳደርበት የግብርና ኢኮኖሚ አካባቢው ካለበት የመሬት ጥበትና የህዝብ ብዛት አንፃር እየተጣጣመ አለመምጣቱ፣ የአካባቢው ተወላጆች ስራ ፍለጋ ወደ ሌላ ቦታ እንዲንቀሣቀሱ ማስገደዱን የጠቆመው ፓርቲው፤ በቀጣይ በአካባቢው ያለው ፖሊሲ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ተኮር መሸጋገር እንደሚገባው ገልጿል፡፡ በወላይታ ለአንድ አርሶ አደር የሚደርሠው መሬት በአማካይ ከ0.13 ሄክታር በታች መሆኑን የጠቀሠው መግለጫው፤ በትንሹ ሶስት ልጆች ያሉት አባወራ፣ ቤተሠቡን መቀለብ እንኳ አይችልም ብሏል፡፡ ለዚህ መፍትሄው የወላይታ ህዝብ ራስን ችሎ በክልል እንዲተዳደር ማድረግና በአካባቢው ኢንዱስትሪ መር ፖሊሲን መተግበር ነው ብሏል፡፡ፓርቲው ግጭቱን ባወገዘበት መግለጫው፤ ህይወት ያጠፉ በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱና ሃብት ለወደመባቸው ተገቢ ካሣ እንዲከፈላቸው ጠይቋል፡፡ ከዚሁ ጉዳዩ ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፤ ከሠኞ እስከ ረቡዕ በሃዋሣ፣ በወላይታ ሶዶና በወልቂጤ ከተማ ባጋጠሙ ግጭቶች ላይ ከህዝብ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸው ወቅት ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል በሶስቱም ዞኖች “ራሳችንን ችለን ክልል እንሁን” የሚለው ይገኝበታል፡፡ በሲዳማ፣ በወላይታና በጉራጌ ማህበረሠቦች ራሣችን ችለን ክልል እንሁን የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄው ህጋዊ መሆኑን ጠቅሠው በቅርቡ አጠቃላይ የሃገሪቱ የወሠንና የክልሎችን ጉዳይ ፈትሾ፣ መፍትሄ የሚያበጀ ኮሚሽን ይቋቋማል ብለዋል።በየወረዳውና ዞኖቹ ግጭቶቹ ሲከሠቱና የሠው ህይወት ሲጠፋ በቸልታ የተመለከቱ አመራሮችም በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣን መልቀቅ እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሣስበዋል፡፡በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የአማራ ክልል ተወላጆችን ያፈናቀሉ ባለስልጣናትም ለህግ እንደሚቀርቡ የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የክልሉ ፕሬዚዳንት እኒህን አመራሮች ከስልጣን ያወርዳሉ ብለው እንደሚያምኑ አስታውቀዋል፡፡ ይህን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የስልጣን ልቀቁ ጥያቄ ተከትሎ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትላቸው ጨምሮ አምስት ከፍተኛ ባለስልጣናት በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣን ለቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ስልጣን መልቀቃቸው ተገቢ እና አርአያነት ያለው ነው ሌሎችም ይለቃሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል፡፡ሃዋሳ ላይ በተፈጠረው ግጭት 10 ሰዎች መሞታቸው እና በሺዎች መፈናቀላቸው እንዲሁም በወልቂጤ 5 ሰዎች መሞታቸው መገለፁ ይታወቃል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የወላይታ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር የሃዋሳውን ግጭት አወገዘ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> - ጠ/ሚኒስትሩ ህዝብ የሚያፈናቅሉ ከስልጣናቸው እንዲወርዱ አሳሰቡ<br /> - ሲዳማ፣ ወላይታ፣ ጉራጌ ዞን ራሣቸውን ችለው ክልል እንዲሆኑ ጥያቄ ቀርቧ...
    0 Comments 0 Shares
  • የሙስሊሙ ኅብረተሰብ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በግንባር ለማነጋገር ጥያቄ አቀረበ
    ታምሩ ጽጌ
    Sun, 06/24/2018 - 17:15
    የሙስሊሙ ኅብረተሰብ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በግንባር ለማነጋገር ጥያቄ አቀረበ ታምሩ ጽጌ Sun, 06/24/2018 - 17:15
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    የሙስሊሙ ኅብረተሰብ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በግንባር ለማነጋገር ጥያቄ አቀረበ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    ከስድስት ዓመታት በፊት የተቋቋመው የሙስሊሙ ኅብረተሰብ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በግንባር እንዲያነጋግሩት ጥያቄ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • በጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥጋና ሠልፍ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 154 ሰዎች ተጎዱ
    ዳዊት እንደሻው
    Sun, 06/24/2018 - 16:55
    በጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥጋና ሠልፍ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 154 ሰዎች ተጎዱ ዳዊት እንደሻው Sun, 06/24/2018 - 16:55
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    በጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥጋና ሠልፍ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 154 ሰዎች ተጎዱ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    ቅዳሜ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን (ዶ/ር) የሥራ እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ በተደረገ ሠልፍ ላይ በፈነዳ ቦምብ፣ የሰው ሕይወት ሲያልፍ 154 ሰዎች ተጎድተዋል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • የፖለቲካ መብቶችን አፍነዋል የተባሉ ሕጎችንና የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻል ብሔራዊ ምክር ቤት ተቋቋመ
    ዮሐንስ አንበርብር
    Sun, 06/24/2018 - 16:52
    የፖለቲካ መብቶችን አፍነዋል የተባሉ ሕጎችንና የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻል ብሔራዊ ምክር ቤት ተቋቋመ ዮሐንስ አንበርብር Sun, 06/24/2018 - 16:52
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    የፖለቲካ መብቶችን አፍነዋል የተባሉ ሕጎችንና የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻል ብሔራዊ ምክር ቤት ተቋቋመ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    የፖለቲካ መብቶችን አፍነዋል ተብለው የተለዩ ሕጎችን ለማሻሻልና መሠረታዊ የፍትሕ ሥርዓት ለውጥ ለማካሔድ የሚሠራ ብሔራዊ ምክር ቤት ተቋቋመ። ምክር ቤቱ "የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ማሻሻያ ብሔራዊ ምክር ቤት" የሚል መጠሪያ የተሰጠው መሆኑን፣ በጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ሰብሳቢነት እንደሚመራ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጮች ተናግረዋል።
    0 Comments 0 Shares