• በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የ“አርበኞች ግንቦት 7” ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ስልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው፣ ከእስር እንዳስፈቷቸው ሰሞኑን ተናገሩ፡፡ ከ4 ዓመታት እስር በኋላ ባለፈው ግንቦት 22 ቀን 2010 ዓ.ም ከማረሚያ ቤት የተለቀቁት የሞት ፍርደኛው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ከቢቢሲ “ሃርድ ቶክ” አዘጋጇ ዘይናብ በደዊ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “አንዳርጋቸው ፅጌን ልቀቁ፤ አለበለዚያ እኔ ስልጣኔን እለቃለሁ” በማለት፤ ሥልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው፣ ከእስር እንዳስፈቷቸው አስረድተዋል፡፡ ከእስር ከተፈቱ በኋላም ለአንድ ሰዓት ተኩል ያህል በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ለቢቢሲ የገለፁት አቶ አንዳርጋቸው፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኔን ለማስፈታት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ተገንዝቤያለሁ” ብለዋል፡፡ ዶ/ር አብይ በኔ ከእስር የመፈታት ጉዳይ፣ ከድርጅታቸው አመራሮች ተቃውሞ  እንደገጠማቸው ተረድቻለሁ ያሉት አቶ አንዳርጋቸው፤ በመጨረሻም  “የማትፈቱት ከሆነ ስልጣኔን እለቃለሁ” ማለታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደነገሯቸው ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየወሰዷቸው ያሉ የፖለቲካ ማሻሻያዎች፤ የሚበረታቱና ሊደገፉ የሚገባቸው ናቸው ብለዋል - አቶ አንዳርጋቸው ከቢቢሲ “ሃርድ ቶክ” ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ።
    በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የ“አርበኞች ግንቦት 7” ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ስልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው፣ ከእስር እንዳስፈቷቸው ሰሞኑን ተናገሩ፡፡ ከ4 ዓመታት እስር በኋላ ባለፈው ግንቦት 22 ቀን 2010 ዓ.ም ከማረሚያ ቤት የተለቀቁት የሞት ፍርደኛው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ከቢቢሲ “ሃርድ ቶክ” አዘጋጇ ዘይናብ በደዊ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “አንዳርጋቸው ፅጌን ልቀቁ፤ አለበለዚያ እኔ ስልጣኔን እለቃለሁ” በማለት፤ ሥልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው፣ ከእስር እንዳስፈቷቸው አስረድተዋል፡፡ ከእስር ከተፈቱ በኋላም ለአንድ ሰዓት ተኩል ያህል በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ለቢቢሲ የገለፁት አቶ አንዳርጋቸው፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኔን ለማስፈታት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ተገንዝቤያለሁ” ብለዋል፡፡ ዶ/ር አብይ በኔ ከእስር የመፈታት ጉዳይ፣ ከድርጅታቸው አመራሮች ተቃውሞ  እንደገጠማቸው ተረድቻለሁ ያሉት አቶ አንዳርጋቸው፤ በመጨረሻም  “የማትፈቱት ከሆነ ስልጣኔን እለቃለሁ” ማለታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደነገሯቸው ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየወሰዷቸው ያሉ የፖለቲካ ማሻሻያዎች፤ የሚበረታቱና ሊደገፉ የሚገባቸው ናቸው ብለዋል - አቶ አንዳርጋቸው ከቢቢሲ “ሃርድ ቶክ” ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ።
    ADDISADMASSNEWS.COM
    “ጠ/ሚሩ ስልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው ነው ያስፈቱኝ” - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የ“አርበኞች ግንቦት 7” ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ስልጣናቸውን ለድርድር አቅርበው፣...
    0 Comments 0 Shares
  •  “አረና” የአልጀርሱ ስምምነት እንዲሠረዝ የሚጠይቅ ሠላማዊ ሰልፍ ዛሬ በመቐሌ ያካሂዳል    አረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉአላዊነት (አረና) የአልጀርሡ ስምምነት ተሰርዞ አዲስ ድርድር እንዲካሄድ የሚጠይቅ ሠላማዊ ሠልፍ ዛሬ በመቐሌ ከተማ ሮማናት አደባባይ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ አረና በመቐሌ ከተማ በሮማናት አደባባይ ለሚያደርገው ሠላማዊ ሠልፍ፣ የእውቅና ጥያቄ፣ ከስድስት ቀናት በፊት ለከተማ አስተዳደሩ አስገብቷል፡፡በዚህ ሠላማዊ ሠልፍ ላይ የአልጀርሱን ስምምነት አስመልክቶ፤ ፓርቲው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ያሣለፈው ውሣኔ የሃገሪቱን ሉአላዊነትና ጥቅም የማያስከብር በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ እንዲሠረዝ እንደሚጠየቅ አስታውቀዋል - አቶ ጎይቶም፡፡ “የአልጀርሡ ስምምነት አስቀድሞ በኤርትራ መንግስት ፈርሷል” ያለው ፓርቲው፤ “በኢትዮጵያ በኩል ይህን የፈረሠ ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ ተገቢነት የለውም ብሏል፡፡በባድመ አካባቢ የሚኖሩ የኢሮብ ማህበረሰቦች፣ በኢህአዴግ ውሣኔ ከፍተኛ ቅሬታ እያቀረቡ መሆኑን የገለፁት አቶ ጎይቶም፤ ሕዝቡ አስቀድሞ አዲግራትን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ሠላማዊ ሠልፍ እያደረገ መሠንበቱን አስታውሰዋል፡፡የአልጀርሡ ስምምነት ፈርሶ የአሠብን ጉዳይና ሌሎች የኢትዮጵያን ሉአላዊ ጥቅሞች ያካተቱ አዲስ ስምምነት መደረግ አለበት ብሎ እንደሚያምንም አረና አስገንዝቧል፡፡ ከሠሞኑ በባድመና አካባቢዋ በሚገኙ ከተሞች፣ ህዝባዊ ሠላማዊ ሠልፎች ሲካሄድ የሠነበቱ ሲሆን በሠልፎቹ ላይም “እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፤ ኤርትራዊ መሆን አንችልም፤ ‹ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኤርትራዊ መሆን የለብንም›፤ “እቃ እንጂ ሰውና አገር አይሸጥም” የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ተሰምተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዜና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኢሮብ ማህበረሰብ ተወላጅ ባለሀብቶች፣ ምሁራንና ግለሰቦች የአልጀርሱን ስምምነት በመቃወም በነገው ዕለት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡
     “አረና” የአልጀርሱ ስምምነት እንዲሠረዝ የሚጠይቅ ሠላማዊ ሰልፍ ዛሬ በመቐሌ ያካሂዳል    አረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉአላዊነት (አረና) የአልጀርሡ ስምምነት ተሰርዞ አዲስ ድርድር እንዲካሄድ የሚጠይቅ ሠላማዊ ሠልፍ ዛሬ በመቐሌ ከተማ ሮማናት አደባባይ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ አረና በመቐሌ ከተማ በሮማናት አደባባይ ለሚያደርገው ሠላማዊ ሠልፍ፣ የእውቅና ጥያቄ፣ ከስድስት ቀናት በፊት ለከተማ አስተዳደሩ አስገብቷል፡፡በዚህ ሠላማዊ ሠልፍ ላይ የአልጀርሱን ስምምነት አስመልክቶ፤ ፓርቲው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ያሣለፈው ውሣኔ የሃገሪቱን ሉአላዊነትና ጥቅም የማያስከብር በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ እንዲሠረዝ እንደሚጠየቅ አስታውቀዋል - አቶ ጎይቶም፡፡ “የአልጀርሡ ስምምነት አስቀድሞ በኤርትራ መንግስት ፈርሷል” ያለው ፓርቲው፤ “በኢትዮጵያ በኩል ይህን የፈረሠ ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ ተገቢነት የለውም ብሏል፡፡በባድመ አካባቢ የሚኖሩ የኢሮብ ማህበረሰቦች፣ በኢህአዴግ ውሣኔ ከፍተኛ ቅሬታ እያቀረቡ መሆኑን የገለፁት አቶ ጎይቶም፤ ሕዝቡ አስቀድሞ አዲግራትን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ሠላማዊ ሠልፍ እያደረገ መሠንበቱን አስታውሰዋል፡፡የአልጀርሡ ስምምነት ፈርሶ የአሠብን ጉዳይና ሌሎች የኢትዮጵያን ሉአላዊ ጥቅሞች ያካተቱ አዲስ ስምምነት መደረግ አለበት ብሎ እንደሚያምንም አረና አስገንዝቧል፡፡ ከሠሞኑ በባድመና አካባቢዋ በሚገኙ ከተሞች፣ ህዝባዊ ሠላማዊ ሠልፎች ሲካሄድ የሠነበቱ ሲሆን በሠልፎቹ ላይም “እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፤ ኤርትራዊ መሆን አንችልም፤ ‹ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኤርትራዊ መሆን የለብንም›፤ “እቃ እንጂ ሰውና አገር አይሸጥም” የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ተሰምተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዜና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኢሮብ ማህበረሰብ ተወላጅ ባለሀብቶች፣ ምሁራንና ግለሰቦች የአልጀርሱን ስምምነት በመቃወም በነገው ዕለት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የአሰብን ጉዳይ ያካተተ አዲስ ስምምነት ያስፈልጋል ተባለ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> “አረና” የአልጀርሱ ስምምነት እንዲሠረዝ የሚጠይቅ ሠላማዊ ሰልፍ ዛሬ በመቐሌ ያካሂዳል<br /><br /> አረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉአላዊ...
    0 Comments 0 Shares
  •       ላለፉት 26 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኢምባሲ በቁም እስር  ላይ የቆዩት ሁለት ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሠቦቻቸው ጋር ሊቀላቀሉ መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡የ82 አመቱ አዛውንት ሌተና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ እና የ74 አመቱ ሌተና ጄነራል አዲስ ተድላ በህዳር 2010 ዓ.ም ከተጠለሉበት የጣሊያን ኢምባሲ በምህረት ወጥተው ከቤተሠቦቻቸው እንዲቀላቀሉ የተለያዩ አካላት ለመንግስት ጥያቄ ማቅረባቸው የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት መንግስት በምህረት ሊፈታቸው የህግ ሂደቶች መጀመራቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ጉዳያቸው ከሠሞኑ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ቀርቦ፣ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ለፓርላማው ውሣኔ ይቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅም ለማወቅ ተችሏል፡፡አዲስ አድማስ ጋዜጣ በህዳር 30 2010 እትሙ፣ ሁለቱ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ባቀረበው ዘገባ፤ ምንም እንኳ ኢምባሲው ለረዥም ዓመታት ከለላ ቢሰጣቸውም ከቤተሠቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር የመገናኘት ዕድል ስለሌላቸው ለከፍተኛ አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት መዳረጋቸውን ጠቁሟል፡ ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ባየህ በመጨረሻዎቹ የደርግ የስልጣን ዘመናት፣ የመንግስት ም/ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩ ሲሆን ሌ/ጀነራል አዲስ ተድላ በበኩላቸው፣ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በቅርቡ በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው መንፈስ አነቃቂ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር “በኤምባሲ ውስጥ ታስረው የሚገኙ የቀድሞ መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይቅርታ አድርገንላቸው ሊወጡ ይገባል” ማለታቸው ይታወሳል፡፡
          ላለፉት 26 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኢምባሲ በቁም እስር  ላይ የቆዩት ሁለት ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሠቦቻቸው ጋር ሊቀላቀሉ መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡የ82 አመቱ አዛውንት ሌተና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ እና የ74 አመቱ ሌተና ጄነራል አዲስ ተድላ በህዳር 2010 ዓ.ም ከተጠለሉበት የጣሊያን ኢምባሲ በምህረት ወጥተው ከቤተሠቦቻቸው እንዲቀላቀሉ የተለያዩ አካላት ለመንግስት ጥያቄ ማቅረባቸው የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት መንግስት በምህረት ሊፈታቸው የህግ ሂደቶች መጀመራቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ጉዳያቸው ከሠሞኑ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ቀርቦ፣ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ለፓርላማው ውሣኔ ይቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅም ለማወቅ ተችሏል፡፡አዲስ አድማስ ጋዜጣ በህዳር 30 2010 እትሙ፣ ሁለቱ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ባቀረበው ዘገባ፤ ምንም እንኳ ኢምባሲው ለረዥም ዓመታት ከለላ ቢሰጣቸውም ከቤተሠቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር የመገናኘት ዕድል ስለሌላቸው ለከፍተኛ አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት መዳረጋቸውን ጠቁሟል፡ ሌተናል ኮለኔል ብርሃኑ ባየህ በመጨረሻዎቹ የደርግ የስልጣን ዘመናት፣ የመንግስት ም/ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩ ሲሆን ሌ/ጀነራል አዲስ ተድላ በበኩላቸው፣ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በቅርቡ በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው መንፈስ አነቃቂ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር “በኤምባሲ ውስጥ ታስረው የሚገኙ የቀድሞ መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይቅርታ አድርገንላቸው ሊወጡ ይገባል” ማለታቸው ይታወሳል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    በጣሊያን ኤምባሲ የሚገኙት 2ቱ የደርግ ባለስልጣናት ከቤተሠቦቻቸው ሊቀላቀሉ ነው - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> ላለፉት 26 አመታት አዲስ አበባ በሚገኘው የጣሊያን ኢምባሲ በቁም እስር ላይ የቆዩት ሁለት ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሠቦቻቸው ጋር...
    0 Comments 0 Shares
  •  “መግለጫው እርስበርሱ የሚጣረስና ግራ የተጋባ ነው” - አረና   የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ በኢትዮ - ኤርትራ የድንበር ግጭትና በኢኮኖሚ የማሻሻያ እርምጃ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ፣ ስብሰባ የተቀመጠው የህውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፤ ኢህአዴግ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ የጠየቀ ሲሆን የግንባሩንም መግለጫ አብጠልጥሏል፡፡ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫም፤ “ኢህአዴግ የአመራር ብልሹነት አጋጥሞታል፤ የድርጅቱ አብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመር አደጋ ላይ ወድቋል” ሲል በስጋት የታጀበ ትችት ሰንዝሯል፡፡ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በስብሰባው፣ በመጋቢት 2010 የም/ቤት ስብሰባ ላይ የተላለፉ ውሣኔዎች የደረሡበትን ደረጃ ሊመለከት ይገባው ነበር ያለው ህውሓት፣ ምክር ቤቱ በወቅቱ ያስቀመጣቸው ድርጅቱን ከአደጋ የማዳኛ መንገዶችና አቅጣጫዎች አሁንም በጥብቅ ዲሲፒሊንና ተጠያቂነት ሊተገበሩ ይገባል ብሏል፡፡ የኢትዮጵያና የኤርትራ የ18 አመታት ግጭት በሠላማዊ መንገድ እንዲፈታ እንዲሁም የመንግስት የልማት ድርጅቶችን አስመልክቶ የወጣው መግለጫ ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፖሊሲ ጋር የሚቃረን አለመሆኑን የጠቆመው የህወኃት ማዕከላዊ ኮሚቴ፤ አፈፃፀሙ ግን በጥንቃቄ መከናወን እንዳለበት አሳስቧል፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጉዳይ ላይ የተሠጠው ውሣኔ ለህዝብ ይፋ መደረግ አልነበረበትም ያለው ድርጅቱ፤ በመጀመሪያ ህዝቡ ሊውያይበት ይገባ ነበር ብሏል፡፡ በጉዳዩ ላይ አጋር ድርጅቶችም መወያየት እንደነበረባቸው በመጠቆም፡፡በዚሁ የአቋም መግለጫ በዴሞክራሲ ሃይሎችና በጥገኝነት መካከል ቀጣይ ትግል ይደረጋል ያለው ህወሓት፤ “ህገ መንግስቱ በሚገባ መልስ የሰጠባቸውን የማንነትና የወሰን ጥያቄዎች፣ ፌደራላዊ ስርአቱን በመፃረርና የህዝቡን ክብር በሚነካ መልኩ በሃይልና በተፅዕኖ፣ የትግራይ ህዝብን አንድነትና ሠላም ለመረበሽ እየተደረጉ ያሉ ፀረ ዲሞክራሲ እንቅስቃሴዎችን ከህዝቡ ጋር በመሆን በፅናት እታገላለሁ ብሏል፡፡ልማታዊ ዲሞክራሲያዊ መስመራችን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አደጋ ውስጥ ወድቋል የሚለው ድርጅቱ፤ የኢህአዴግ አመራር አብዮታዊ ዲሞክራሲ ባህሪው እየተሸረሸረ በከፋ የጥገኛ ዝቅጠት አረንቋ ውስጥ መዘፈቁን አስታውቋል። ለአብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመር ወድቀትም አመራሩ ተጠያቂ ነው ብሏል- ህወኃት በመግለጫው፡፡አንዳንድ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ውሳኔዎችን በመግለጫው ያብጠለጠለው ህወሓት፤ በድርጅቱ ውስጥ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በግልፅ እየታየ የመጣውን የአመራር ብልሹነት መመልከት ይገባው ነበር ብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ደረጃ እየተደረጉ ያሉ የአመራር ምደባዎች የኢህአዴግን ህገ-ደንብና ተቋማዊ አሠራር ያልተከተሉ ናቸው ሲል በመተቸትም፤ የአመራር ምደባዎቹ እንዲታረሙ ጠይቋል፡፡ ለድርጅቱ ነባር አመራሮች እውቅና እንዲሠጥም ህወሓት ጠይቋል፡፡የትግራይ ህዝብና መሪ ድርጅቱ ህወኃት፤ እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመራችን አስተማማኝ ደጀን በመሆን፣ ትግሉን ያጠናከራል ብሏል በመግለጫው፡፡ ሠላማዊ ህጋዊ መንገድ ተከትለው አማራጭ ሃሣብ ከሚያቀረቡ ሃይሎች ጋር አብሮ እንደሚሠራ የጠቆመው ድርጅቱ፤ ህውሓትንና የትግራይን ህዝብ ለማዳከምና ለመምታት በተለያዩ መንገዶች፣ ፀረ-ትግራይ ህዝብና ፀረ-ህወኃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የውስጥም የውጭም ሃይሎችን ህዝቡ አምርሮ እንዲታገላቸው ጥሪ አቅርቧል፡፡የህወሓትን መግለጫ አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለአዲስ አድማስ የሰጡት የአረና ትግራይ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ፤ መግለጫው እርስ በእርሡ የሚጣረስና ግራ የተጋባ ነው ብለዋል፡፡“ህወኃት የተቃወመው አንድ ነገር ቢኖር፣ የህዝብ ድጋፍ ያለው የባለስልጣናት በጡረታ መሰናበትን ነው” የሚሉት አቶ ጎይቶኦም፤ መግለጫው በኤርትራ ጉዳይና በልማት ድርጅቶች ላይ ህወኃት ከኢህአዴግ የተለየ አቋም እንዳላንፀባረቀ ያመላክታል ብለዋል፡፡
     “መግለጫው እርስበርሱ የሚጣረስና ግራ የተጋባ ነው” - አረና   የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ በኢትዮ - ኤርትራ የድንበር ግጭትና በኢኮኖሚ የማሻሻያ እርምጃ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ፣ ስብሰባ የተቀመጠው የህውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፤ ኢህአዴግ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ የጠየቀ ሲሆን የግንባሩንም መግለጫ አብጠልጥሏል፡፡ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫም፤ “ኢህአዴግ የአመራር ብልሹነት አጋጥሞታል፤ የድርጅቱ አብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመር አደጋ ላይ ወድቋል” ሲል በስጋት የታጀበ ትችት ሰንዝሯል፡፡ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በስብሰባው፣ በመጋቢት 2010 የም/ቤት ስብሰባ ላይ የተላለፉ ውሣኔዎች የደረሡበትን ደረጃ ሊመለከት ይገባው ነበር ያለው ህውሓት፣ ምክር ቤቱ በወቅቱ ያስቀመጣቸው ድርጅቱን ከአደጋ የማዳኛ መንገዶችና አቅጣጫዎች አሁንም በጥብቅ ዲሲፒሊንና ተጠያቂነት ሊተገበሩ ይገባል ብሏል፡፡ የኢትዮጵያና የኤርትራ የ18 አመታት ግጭት በሠላማዊ መንገድ እንዲፈታ እንዲሁም የመንግስት የልማት ድርጅቶችን አስመልክቶ የወጣው መግለጫ ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፖሊሲ ጋር የሚቃረን አለመሆኑን የጠቆመው የህወኃት ማዕከላዊ ኮሚቴ፤ አፈፃፀሙ ግን በጥንቃቄ መከናወን እንዳለበት አሳስቧል፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጉዳይ ላይ የተሠጠው ውሣኔ ለህዝብ ይፋ መደረግ አልነበረበትም ያለው ድርጅቱ፤ በመጀመሪያ ህዝቡ ሊውያይበት ይገባ ነበር ብሏል፡፡ በጉዳዩ ላይ አጋር ድርጅቶችም መወያየት እንደነበረባቸው በመጠቆም፡፡በዚሁ የአቋም መግለጫ በዴሞክራሲ ሃይሎችና በጥገኝነት መካከል ቀጣይ ትግል ይደረጋል ያለው ህወሓት፤ “ህገ መንግስቱ በሚገባ መልስ የሰጠባቸውን የማንነትና የወሰን ጥያቄዎች፣ ፌደራላዊ ስርአቱን በመፃረርና የህዝቡን ክብር በሚነካ መልኩ በሃይልና በተፅዕኖ፣ የትግራይ ህዝብን አንድነትና ሠላም ለመረበሽ እየተደረጉ ያሉ ፀረ ዲሞክራሲ እንቅስቃሴዎችን ከህዝቡ ጋር በመሆን በፅናት እታገላለሁ ብሏል፡፡ልማታዊ ዲሞክራሲያዊ መስመራችን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አደጋ ውስጥ ወድቋል የሚለው ድርጅቱ፤ የኢህአዴግ አመራር አብዮታዊ ዲሞክራሲ ባህሪው እየተሸረሸረ በከፋ የጥገኛ ዝቅጠት አረንቋ ውስጥ መዘፈቁን አስታውቋል። ለአብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመር ወድቀትም አመራሩ ተጠያቂ ነው ብሏል- ህወኃት በመግለጫው፡፡አንዳንድ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ውሳኔዎችን በመግለጫው ያብጠለጠለው ህወሓት፤ በድርጅቱ ውስጥ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በግልፅ እየታየ የመጣውን የአመራር ብልሹነት መመልከት ይገባው ነበር ብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ደረጃ እየተደረጉ ያሉ የአመራር ምደባዎች የኢህአዴግን ህገ-ደንብና ተቋማዊ አሠራር ያልተከተሉ ናቸው ሲል በመተቸትም፤ የአመራር ምደባዎቹ እንዲታረሙ ጠይቋል፡፡ ለድርጅቱ ነባር አመራሮች እውቅና እንዲሠጥም ህወሓት ጠይቋል፡፡የትግራይ ህዝብና መሪ ድርጅቱ ህወኃት፤ እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመራችን አስተማማኝ ደጀን በመሆን፣ ትግሉን ያጠናከራል ብሏል በመግለጫው፡፡ ሠላማዊ ህጋዊ መንገድ ተከትለው አማራጭ ሃሣብ ከሚያቀረቡ ሃይሎች ጋር አብሮ እንደሚሠራ የጠቆመው ድርጅቱ፤ ህውሓትንና የትግራይን ህዝብ ለማዳከምና ለመምታት በተለያዩ መንገዶች፣ ፀረ-ትግራይ ህዝብና ፀረ-ህወኃት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የውስጥም የውጭም ሃይሎችን ህዝቡ አምርሮ እንዲታገላቸው ጥሪ አቅርቧል፡፡የህወሓትን መግለጫ አስመልክቶ አስተያየታቸውን ለአዲስ አድማስ የሰጡት የአረና ትግራይ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ፤ መግለጫው እርስ በእርሡ የሚጣረስና ግራ የተጋባ ነው ብለዋል፡፡“ህወኃት የተቃወመው አንድ ነገር ቢኖር፣ የህዝብ ድጋፍ ያለው የባለስልጣናት በጡረታ መሰናበትን ነው” የሚሉት አቶ ጎይቶኦም፤ መግለጫው በኤርትራ ጉዳይና በልማት ድርጅቶች ላይ ህወኃት ከኢህአዴግ የተለየ አቋም እንዳላንፀባረቀ ያመላክታል ብለዋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ህውሓት፤ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚን መግለጫ አብጠለጠለ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> “መግለጫው እርስበርሱ የሚጣረስና ግራ የተጋባ ነው” - አረና<br /><br /> የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ በኢትዮ - ኤርትራ የድንበር ግጭትና...
    0 Comments 0 Shares
  • ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከል ተሹመዋል                     የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል አዳዲስ ዳይሬክተሮችን አገኘ፡፡ በዚሁ መሰረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ጥበባት ትምህርት ክፍል ዲን በመሆን ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የነበሩት ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርን ለረጅም ዓመታት የመሩት አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከልነት ዳይሬክተርነት ተሹመዋል፡፡ ሹመቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደምብ ቁጥር 2574/2003 አንቀፅ 7(1) መሰረት የተካሄደና የሹመቱ ደብዳቤ በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ የፀደቀ መሆኑም ታውቋል፡፡ ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ በሹመቱ ምን እንደተሰማቸው ተጠይቀው ሲመልሱ “ቴአትር የጀመርኩት በ12 ዓመቴ ነው፡፡ ህይወቴ ከሙያው ጋር የተቆራኘ ነው” ካሉ በኋላ፣ በየትኛውም ዓለም ያለ የቴአትር ባለሙያ የመጨረሻ ግቡ የአገሩን ብሔራዊ ቴአትር ማገልገል ነው እኔም የአገሬን ብሔራዊ ቴአትር እንዳገለግል በመመረጤ ደስታና ክብር ተሰምቶኛል ብለዋል፡፡  “አቶ ተስፋዬ ሽመልስ በበኩላቸው የተሾምኩበት ቦታ እንደ ባለሙያ ትልቅ ቦታ ነው” ያሉ ሲሆን በስራ ቆይታዬ በሌሎች አለማት ያየኋቸውን የባህል ማዕከላት አገሬ ላይ እውን ለማድረግ እሰራለሁ ብለዋል፡፡ አክለውም ቦታው የአንድን አገር ባህል ለማሳደግ ታሪካችንን ለማጉላት እና ያሉንን ጠንካራና የጋራ እሴቶች ለማጉላት ብዙ የሚያሰራ በመሆኑ በቦታው ላይ በመሾሜ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡
    ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከል ተሹመዋል                     የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል አዳዲስ ዳይሬክተሮችን አገኘ፡፡ በዚሁ መሰረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ጥበባት ትምህርት ክፍል ዲን በመሆን ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የነበሩት ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርን ለረጅም ዓመታት የመሩት አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከልነት ዳይሬክተርነት ተሹመዋል፡፡ ሹመቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደምብ ቁጥር 2574/2003 አንቀፅ 7(1) መሰረት የተካሄደና የሹመቱ ደብዳቤ በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ የፀደቀ መሆኑም ታውቋል፡፡ ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ በሹመቱ ምን እንደተሰማቸው ተጠይቀው ሲመልሱ “ቴአትር የጀመርኩት በ12 ዓመቴ ነው፡፡ ህይወቴ ከሙያው ጋር የተቆራኘ ነው” ካሉ በኋላ፣ በየትኛውም ዓለም ያለ የቴአትር ባለሙያ የመጨረሻ ግቡ የአገሩን ብሔራዊ ቴአትር ማገልገል ነው እኔም የአገሬን ብሔራዊ ቴአትር እንዳገለግል በመመረጤ ደስታና ክብር ተሰምቶኛል ብለዋል፡፡  “አቶ ተስፋዬ ሽመልስ በበኩላቸው የተሾምኩበት ቦታ እንደ ባለሙያ ትልቅ ቦታ ነው” ያሉ ሲሆን በስራ ቆይታዬ በሌሎች አለማት ያየኋቸውን የባህል ማዕከላት አገሬ ላይ እውን ለማድረግ እሰራለሁ ብለዋል፡፡ አክለውም ቦታው የአንድን አገር ባህል ለማሳደግ ታሪካችንን ለማጉላት እና ያሉንን ጠንካራና የጋራ እሴቶች ለማጉላት ብዙ የሚያሰራ በመሆኑ በቦታው ላይ በመሾሜ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ብሔራዊ ቴአትርና ብሔራዊ የባህል ማዕከል አዳዲስ ዳይሬክተር አገኙ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከል ተሹመዋል<br /> <br /> የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርና የኢት...
    0 Comments 0 Shares
  • የሃረሪ ክልላዊ መንግስትን ላለፉት 15 አመታት በፕሬዚዳንትነት የመሩት አቶ ሙራድ አብዱላዲ፤ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ፡፡አቶ ሙራድ አብዱላዲ ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ የሃረሪ ክልልን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው የሚታወቅ ሲሆን ከስልጣን የሚለቁበት ምክንያት ግን አልታወቀም፡፡ ምንጮች በበኩላቸው ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ ከክልሉ የህዝብ ተወካዮች ጋር ባካሄዱት ውይይት ላይ በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግር መስፋቱ፣ ብሄርተኝነትና ጎሰኝነት መንሰራፋቱ ይህም የግጭት መንስኤ እየሆነ መምጣቱ በህዝቡ ተነስቶ እሳቸው ላለፉት 15 ዓመታት ከቆዩበት ስልጣን እንዲነሱ መጠየቃቸውን ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሃረር ከተማና አካባቢዋ የተለያዩ ግጭቶችና ተቃውሞዎች ሲከሠቱ የቆዩ ሲሆን ባለፈው ሣምንት ከመሬት ይገባኛል ጥያቄ ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ግጭት፣ በርካቶች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ሲሆን የሆቴል ኢንቨስትመንቶችም ለቃጠሎ መዳረጋቸው ይታወቃል፡፡የክልሉ መንግስት ምክር ቤት፣ አቶ ሙራድን የሚተካውን ቀጣዩን የሃረሪ ክልል ፕሬዚዳንት ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
    የሃረሪ ክልላዊ መንግስትን ላለፉት 15 አመታት በፕሬዚዳንትነት የመሩት አቶ ሙራድ አብዱላዲ፤ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ፡፡አቶ ሙራድ አብዱላዲ ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ የሃረሪ ክልልን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው የሚታወቅ ሲሆን ከስልጣን የሚለቁበት ምክንያት ግን አልታወቀም፡፡ ምንጮች በበኩላቸው ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ ከክልሉ የህዝብ ተወካዮች ጋር ባካሄዱት ውይይት ላይ በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግር መስፋቱ፣ ብሄርተኝነትና ጎሰኝነት መንሰራፋቱ ይህም የግጭት መንስኤ እየሆነ መምጣቱ በህዝቡ ተነስቶ እሳቸው ላለፉት 15 ዓመታት ከቆዩበት ስልጣን እንዲነሱ መጠየቃቸውን ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሃረር ከተማና አካባቢዋ የተለያዩ ግጭቶችና ተቃውሞዎች ሲከሠቱ የቆዩ ሲሆን ባለፈው ሣምንት ከመሬት ይገባኛል ጥያቄ ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ግጭት፣ በርካቶች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ሲሆን የሆቴል ኢንቨስትመንቶችም ለቃጠሎ መዳረጋቸው ይታወቃል፡፡የክልሉ መንግስት ምክር ቤት፣ አቶ ሙራድን የሚተካውን ቀጣዩን የሃረሪ ክልል ፕሬዚዳንት ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የሃረሪ ክልል ፕሬዚዳንት የስልጣን መልቀቂያ አቀረቡ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">የሃረሪ ክልላዊ መንግስትን ላለፉት 15 አመታት በፕሬዚዳንትነት የመሩት አቶ ሙራድ አብዱላዲ፤ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ፡፡<br />አቶ ሙራድ አብ...
    0 Comments 0 Shares
  • በወልቂጤና በሃዋሳ አገርሽተው የሰነበቱ ግጭቶች ከሃሙስ ጀምሮ መረጋጋታቸውን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ መንግስት በበኩሉ፤ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ጠቁሞ፤ የግጭቶቹን መንስኤዎችና ጉዳት አጣርቶ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል፡፡በሁለቱ ከተሞች በተከሠተው ግጭት፣ በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የንብረት ውድመት ማስከተሉንም የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ም/ኮሚሽነር አህመድ ላዲን ጀማል ጠቁመዋል፡፡በሃዋሳ ከተማ ማክሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2010 ዓ.ም የተፈጠረው ግጭት፣ ከሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ የፍቼ ጨንበላላ በዓል ጋር ተያያዥነት ያለው ሲሆን በወልቂጤ የተነሣው ግጭት መነሻ ደግሞ በሁለት የእግር ኳስ ቡድነወ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት መሆኑ ታውቋል።ማዕከሉን ወልቂጤ ከተማ ባደረገው የጉራጌ ዞን ውስጥ የጉራጌ፣ ቀቤናና ማረቆ ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በእግር ኳስ ሠበብ የተነሳው ግጭት፣ ወደ ብሄር ግጭት መዞሩ ታውቋል። በጉራጌና በቀቤና ብሔረሰቦች መካከልም “የወልቂጤ ከተማ ይገባኛል፤ ከተማችንን ለቃችሁ ውጡ” ወደሚል ግጭት ማምራቱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በርካታ መኖሪያ ቤቶችና ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን እስከ ረቡዕ አመሻሽ ድረስም ከአዲስ አበባ ጅማ ያለው የትራንስፖርት አገልግሎት ተስተጓጉሎ መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡ በእነዚህ ግጭቶች የደረሱ አጠቃላይ ጉዳቶች ተጣርተው ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉ የክልሉ መንግስት ያስታወቀ ሲሆን ግጭቶቹ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ መረጋጋታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል፤ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የ3ኛ ዓመት ተማሪዎች፤ “የሆልስቲክ ፈተና አንፈተንም” በሚል ተቃውሞ፣ ባለፈው ሐሙስ ግቢውን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል።
    በወልቂጤና በሃዋሳ አገርሽተው የሰነበቱ ግጭቶች ከሃሙስ ጀምሮ መረጋጋታቸውን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ መንግስት በበኩሉ፤ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ጠቁሞ፤ የግጭቶቹን መንስኤዎችና ጉዳት አጣርቶ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል፡፡በሁለቱ ከተሞች በተከሠተው ግጭት፣ በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የንብረት ውድመት ማስከተሉንም የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ም/ኮሚሽነር አህመድ ላዲን ጀማል ጠቁመዋል፡፡በሃዋሳ ከተማ ማክሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2010 ዓ.ም የተፈጠረው ግጭት፣ ከሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ የፍቼ ጨንበላላ በዓል ጋር ተያያዥነት ያለው ሲሆን በወልቂጤ የተነሣው ግጭት መነሻ ደግሞ በሁለት የእግር ኳስ ቡድነወ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት መሆኑ ታውቋል።ማዕከሉን ወልቂጤ ከተማ ባደረገው የጉራጌ ዞን ውስጥ የጉራጌ፣ ቀቤናና ማረቆ ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በእግር ኳስ ሠበብ የተነሳው ግጭት፣ ወደ ብሄር ግጭት መዞሩ ታውቋል። በጉራጌና በቀቤና ብሔረሰቦች መካከልም “የወልቂጤ ከተማ ይገባኛል፤ ከተማችንን ለቃችሁ ውጡ” ወደሚል ግጭት ማምራቱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በርካታ መኖሪያ ቤቶችና ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን እስከ ረቡዕ አመሻሽ ድረስም ከአዲስ አበባ ጅማ ያለው የትራንስፖርት አገልግሎት ተስተጓጉሎ መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡ በእነዚህ ግጭቶች የደረሱ አጠቃላይ ጉዳቶች ተጣርተው ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉ የክልሉ መንግስት ያስታወቀ ሲሆን ግጭቶቹ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ መረጋጋታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል፤ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የ3ኛ ዓመት ተማሪዎች፤ “የሆልስቲክ ፈተና አንፈተንም” በሚል ተቃውሞ፣ ባለፈው ሐሙስ ግቢውን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል።
    ADDISADMASSNEWS.COM
    በሃዋሳና ወልቂጤ ግጭቶች አገረሹ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">በወልቂጤና በሃዋሳ አገርሽተው የሰነበቱ ግጭቶች ከሃሙስ ጀምሮ መረጋጋታቸውን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ መንግስት በበኩሉ፤ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መ...
    0 Comments 0 Shares
  • የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አልጋ ወራሽ በአዲስ አበባ
    ነአምን አሸናፊ
    Sun, 06/17/2018 - 15:42
    የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አልጋ ወራሽ በአዲስ አበባ ነአምን አሸናፊ Sun, 06/17/2018 - 15:42
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አልጋ ወራሽ በአዲስ አበባ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    ዓርብ ሰኔ 8 ቀን 2010 ዓ.ም. አዲስ አበባ የገቡትን የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ አልጋ ወራሽ ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ አልናህያን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ከተቀበሉ በኋላ ራሳቸው በሚያሽከረክሩት አውቶሞቢል አሳፍረው ወደ ጉብኝት መዳረሻቸው ወስደዋቸዋል፡፡
    0 Comments 0 Shares